ሲጀምሩ ፤
ሁለቱም ቆርኬዎች ፤
አብረው ከኖሩበት ፤
ከሚያምረው መስክ ዳር ፤
እየጋጡ ነበር ፤
ከጨፌው ማሳ ላይ ፤ እየፈነደቁ ፤
ድንገት ሳይታሰብ ፤
እነ ተኩላዎች ፤
ወዳጅ ዘመድ መስለው ፤ ወደዚያ ዘለቁ ።
ሁለቱም ቆርኬዎች ፤
አብረው ከኖሩበት ፤
ከሚያምረው መስክ ዳር ፤
እየጋጡ ነበር ፤
ከጨፌው ማሳ ላይ ፤ እየፈነደቁ ፤
ድንገት ሳይታሰብ ፤
እነ ተኩላዎች ፤
ወዳጅ ዘመድ መስለው ፤ ወደዚያ ዘለቁ ።
ቆርኬዎቹ ዘንተው ፤
ሳር ከሚግጡበት ፤
ደረሱ ተኩላዎች ፤ እየተፋነኑ ፤
ውሃ በሞላው አፍ ፤
የጨፌውን ማማር ፤
የጋጮቹን ገላ ፤ እያስተነተኑ ፤
የተኩላ መንጎች ፤
እንኳን በስጋቸው ፤
በተቆላለፈው ፣ በቀንዳቸው ቀኑ ።
ሳር ከሚግጡበት ፤
ደረሱ ተኩላዎች ፤ እየተፋነኑ ፤
ውሃ በሞላው አፍ ፤
የጨፌውን ማማር ፤
የጋጮቹን ገላ ፤ እያስተነተኑ ፤
የተኩላ መንጎች ፤
እንኳን በስጋቸው ፤
በተቆላለፈው ፣ በቀንዳቸው ቀኑ ።
ቆርኬዎቹ ጠግበው ፤ እስኪፈነጥዙ ፤
እነ ተኩላዎች ፤
ሳሩ ላይ ዋሉበት እየተሟዘዙ ።
እነ ተኩላዎች ፤
ሳሩ ላይ ዋሉበት እየተሟዘዙ ።
ጀመሩ ቆርኬዎች ፤
በጥጋብ ጀመሩ ቀጠሉ ማስካካት ፤
ተኩላ ተናቃ ፤
በጨዋታ መሃል ሸር ለማስገባት ።
በጥጋብ ጀመሩ ቀጠሉ ማስካካት ፤
ተኩላ ተናቃ ፤
በጨዋታ መሃል ሸር ለማስገባት ።
እንደዚህ አላቸው ተኩላ አባ ሴራ ፤
ከአያት ቅም አያቶች ታሪክ ስናጣራ ፤
አለቃ ሚሆነው የቆርኬዎች አውራ ፤
ታግሎ የጣለ ነው ፤
ተፋልሞ ሚገዛ ከገጠሙት ጋራ ።
ከአያት ቅም አያቶች ታሪክ ስናጣራ ፤
አለቃ ሚሆነው የቆርኬዎች አውራ ፤
ታግሎ የጣለ ነው ፤
ተፋልሞ ሚገዛ ከገጠሙት ጋራ ።
ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ጠቅልሎ ፤
በቀንዱ ጀመረው ፤
ካንደኛው ትከሻ አንዱ ቆርኬ ዘሎ ።
በቀንዱ ጀመረው ፤
ካንደኛው ትከሻ አንዱ ቆርኬ ዘሎ ።
ተኩላ ዳር ቆማ ፤
በጭብጨባ በአጀብ ፤
በል በለው ትላለች ፤ በክፋት አንደበት ፤
ጀግና ማለት በኛ ፤
የጫካው አርበኛ ፤ የሚዘመርለት ፋኖ እየተባለ ፤
ቀንድን በቀንድ ይዞ ፤
አንገቱን ጠምዝዞ መሬት ላይ የጣለ።
በጭብጨባ በአጀብ ፤
በል በለው ትላለች ፤ በክፋት አንደበት ፤
ጀግና ማለት በኛ ፤
የጫካው አርበኛ ፤ የሚዘመርለት ፋኖ እየተባለ ፤
ቀንድን በቀንድ ይዞ ፤
አንገቱን ጠምዝዞ መሬት ላይ የጣለ።
በግብግብ መሃል ፤
ገራገር ቆርኬዎች ፤
የተኩላን ፊሽካ ፤ ሰምተው ተናነቁ ፤
ቀንዳቸው ተጣልፎ ፤
ሁለቱም ሜዳው ላይ ዘፍ ብለው ወደቁ ።
ገራገር ቆርኬዎች ፤
የተኩላን ፊሽካ ፤ ሰምተው ተናነቁ ፤
ቀንዳቸው ተጣልፎ ፤
ሁለቱም ሜዳው ላይ ዘፍ ብለው ወደቁ ።
በተጠለፈ ቀንድ ፤ በተገመደ አንገት ፤ ወድቀው ተጋጠሙ ፤
ራስ በራሳቸው በጀመሩት ትግል ማንም ሳያሸንፍ ሁለቱም ደከሙ ፤
በተኩላ ተንኮል አብሮ አደግ ቆርኬዎች ሞትን ተሸለሙ ።
ራስ በራሳቸው በጀመሩት ትግል ማንም ሳያሸንፍ ሁለቱም ደከሙ ፤
በተኩላ ተንኮል አብሮ አደግ ቆርኬዎች ሞትን ተሸለሙ ።
ይህን ያየ ቆርኬ ፤
የወንድሞቹ ሞት ፤ በተኩላዎች ሴራ መሆኑን ተረድቶ ፤
ከሞቱበት ሳር ላይ ፤
ካለው ትልቅ ዛፍ ላይ ፤
እንዲህ ብሎ ጻፈ ብእሩን አውጥቶ ።
የወንድሞቹ ሞት ፤ በተኩላዎች ሴራ መሆኑን ተረድቶ ፤
ከሞቱበት ሳር ላይ ፤
ካለው ትልቅ ዛፍ ላይ ፤
እንዲህ ብሎ ጻፈ ብእሩን አውጥቶ ።
ሰፊ መስክ ሳለ ፤
ሰፊ ጨፌ ሳለ ፤ በዚህ በመንደሩ ፤
ያንዲት እናት ልጆች ፤
አንተ ወግድልኝ
እኔ ነኝ አለቃ ፤
እኔ ነኝ ባለ ሹም በሚሉት አምቡላ ስለተሳከሩ ፤
ሞሰቡ ሳይቸግር ፤
እኔ በሚል እሳት ፤ ተበላልተው ቀሩ ።
ሰፊ ጨፌ ሳለ ፤ በዚህ በመንደሩ ፤
ያንዲት እናት ልጆች ፤
አንተ ወግድልኝ
እኔ ነኝ አለቃ ፤
እኔ ነኝ ባለ ሹም በሚሉት አምቡላ ስለተሳከሩ ፤
ሞሰቡ ሳይቸግር ፤
እኔ በሚል እሳት ፤ ተበላልተው ቀሩ ።