Followers

Tuesday, August 9, 2016

ከስርዓት በአድሎዊነት የሚጠቀሙ አድርባዮች እንጂ ህዝብ አይደለም፡፡



የኢትዮጵያን የጦርነት ታሪክ  ወደ ኋላ ስንመረመር የእርስ በእርስ ጦርነቶችን ጨምሮ በወራሪዎች የተሰነዘሩብን ጭምር ተደምረው በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ላይ ያሳረፉት ጫና ቀላል አይደለም፡፡ ራስ አሉላ አባ ነጋ አንዴ ከግብጽ አንዴ ከጣሊያን ወራሪ ሃይል ጋር የኢትዮጵያን የቀይባህር ድንበር በአልሞት ባይ ተጋዳይነት እየታገሉ እስተ እርጅና እድሜአቸው ድረስ ታግልዎል፡፡ በአድዎ ጦርነት ጊዜ የአውዳሚ መሳሪያዎች ጫና ቀላል ቢሆንም ደካማ ኢኮኖሚ ላላት አገራችን በሰውና በንብረት ላይ የደርሰው ጉዳት ቀላል አይደለም፡፡ ምንም እንኳን አንዳን የትግራይ ወንድሞቻችን በባንዳነት ቢሰለፉም እዉነተኛ የትግራይ ልጆችም የተዎደቁለት ድል ነው፡፡  በማይጨው ሽንፈት በተጠናቀቀው የጣሊያን ወረራም ጊዜ ፋሺሰት ጣሊያን የመርዝ ገዝ የሚረጭ ቦምብ በኢትዮጵያዊያን ላይ ሲያዘንብ የትግራይ ህዝብም  ተጠቂ ነበር፡፡ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለማስከበር እና ንጉሳዊ አስተዳደሮ እንዳይገረሰስ እና ሃይማኖት እንዳይረክስ በትግሬ አባቶቻችን የተከፈለው መስዎእትነት ግን ዛሬ በዘመናችን ከትግራይ በመጡ ገዣዎቻችን ተዛብቶ እየተተረጎመ ነው፡፡
አጼ ሚኒሊክ  የሳህለ ስስሴን ንግስና ቆጥረው አንድ ቀን በአያቶቻቸው ዙፋን እንደሚቀመጡ እያሰቡ ቀደም ብሎ ላልቶ የነበረውንና ፤ንጉስ ሳህለስላሴ ያጠነናከሩትን ግዛት የበለጠ እያስፋፉ ንግስናቸው ይጠባበቁ ነበር፡፡ በኋላም የሸዎው ንጉስ የሚለው በአጼ ዮሃንሰ ፀደቀላቸው ፡፡ ኢትዮጵያዊያን መሳፍንት የአገኙትን የሃይል ሚዛን ተጠቅመው ፤ በአብዛኛው ጊዜም ከውጭ ሃይል የሚደረግን ድጋፍ ተገን አድርገው ተቀናቀኞቻቸዉን በማስወገድ የነገሱበት የታሪክ ሂደት አለ፡፡ አፄ ዮሃንስ የእንግሊዘን ጦር መቅደላ በመምራት በአጼ ቴዎድሮስ ሞት እና በመቅደላ በተዘረፉ ቅርሶች ዋጋ በታጠቀዉ መሳሪ  ዋግ ሹም ጎበዜን (እራሳቸውን አጼ ተክለጊዮርጊስ ብለው አንግሰው ነበር) ድለ በማድረግ መንገስ ችለዋል፡፡ ዋግ ሹም ጎበዜ በጊዜው ያላቸውን የሰራዊት ብዛት ለመግለጽ እና አናሳ ሰራዊት ያለው ደጃች ካሳ ምርጫ ጦርነት እንዳሞክር ለማስፈራራት በቁና ሙሉ ጤፍ  አስይዘው ለመልክተኛቸው ቢልኩም ደጃች ካሳ ምርጫ  ቁና ሙሉ ጤፉን አስፈጭተው መልሰው ላኩላቸው፡፡ ዋግ ሹም ጎበዜ ማስፈራራት ቢሞክሩም በምላሹ ግን ሰረዊትህ ቢበዛ እንደ ጤፉ እቆላዎለሁ የሚል መልስ መጣላቸው፡፡ ይህን ታሪክ ተክለፃዲቅ መኩሪያ የኢትዮያ ታሪክ ከአጼ ቴዎደሮስ እስከ አጼ ሃይለስላሴ በሚለው መጽሃፋቸው መዝግበውታል፡፡
ደጃች ካሳ  በኋላ አጼ ዮሃንስ አጼ ተክለጊዮርጊስን፤ የእህታቸውን ባል ድል አርገው ይዘው በወረንጦ አይናቸውን ያወጦቸው በዘመኑ የነበረውን ጭካኔ መገለጫ እንጂ በሙሉ በዎግ ህዝብ ላይ የተካሄደ የዘር ማጥፋት ሊሆን አይችልም፡፡ አፄ ሚኒሊክ ከአድዎ ድል ማግስት በባንዳነት ተሰማርተው የነበሩት የትግራይ ተወላጆች ላይ እርምጃ ወስደዎል፡፡ ምንም እንኳን የአፄ ሚኒሊክ ቸርነተት በአደባባይ የሚታዎቅ እና በታሪክ ደርሳናትም የተመዘገበ ቢሆንም ፤ ንጉሱ በተሰየሙበት የአደባባይ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የትግራይ ባንዶች እጃቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡ የአፄ ሚኒሊክ ዘመን በወታደራዊ ፍርድ ቤት የተወሰደ እርምጃ በመላው የትግራይ ህዝብ ላይ የተወሰደ አድርጓ መውሰድ አንድም በጊዜው የነበረውን ዘመን አለመረዳት ወይም የባንድነትን ታሪክ ለመሸፈን የሚደረግ ሙከራ ነው፡፡

ወታደራዊ ደርግ በተማሪዎች ትግል እና በሰራተኛ ማህበራት አመፃ ኣና ውክቢያ ይላጋ ከነበረውን ንጉሳዊ መንግስተ ስልጣን በመመንተፍ ወደ ስልጣን ሲመጣ፤ በተማሪዎች ትግል ውስጥ አብረው ይሳተፉ የነበሩት ከፊል የትግራይ ልጆች ኢትዮጵያ ብሄርተኝነትን በማቀንቀን ከኢትዮጵያ ወንድሞቻቸው ጋር አንድ በመሆን የጋራ ትግል ለማካሄድ ቃል በመግባት ሕዝባዊ መንግስት ለመመስረት ብዙ ደክመዎል፡፡ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ቁማር ፤ ቀዝቃዛው ጦርነት እና እርስ በርሰ የመጠላለፍ ፖለቲካ ኢህአፓንና እና መኢሶንን የመሰሉ ኢትጵያዊ ድርጅቶችን ከመስመር አስወጥቶ ሕወሃት ለተባለ ጠባብ ዘረኛ ቡድን መንገድ ጠርጎለታል፡፡
ተኃሕት ቆይቶም ሕወሃት የተባለው ፤ ማገብት፤ ሻብያ እና ጀብሃ በሚባሉት ድርጅቶች ጥላ ስር የተሰበሰቡት የሰሜን ኢትዮጵያ ልጆች የሄዱበት መንገድ ግን ከመጀሪያዉ የኢትዮጵያን መሰረት የናደ ነበር፡፡ ለረዥም ዘመን ሉዓላዊነቶን ጠብቃ ፤ እንደ ሃገር በንጉሶቾ በማእከላዊ አስተዳደር እየተመራች የቋየችን ሃገር ታሪክ ወደጎን በማደረግ የኢትየጵያ ታሪክ የ100 ዓመት ታሪክ ነው ፤ ህዳሴዎ ዛሬ እራሱን ኢህአዴግ ብሎ የሚጠራው እንዳበሰረላት ገዢው ቡድን ይናገራል፡፡
በተለያዩ ሃገራት ታሪክ የህዝቦች የጭቋና ታሪክ የባርነት ፍንገላን ጨምሮ የታሪካችን አካል ቢሆንም ፤ የኢትዮጵያን ህዝብ ያለፈ ታሪክ እስረኛ እንድንሆን ከጥዎት ጀምረው በዘር ላይ የተመሰረተ ፖሊሳቸውን እየተገበሩ ይገኛሉ፡፡ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነት የሚደክም ማንኛዉም ግለሰብ እንደሚረዳው በገዢዎቸ ጭቋና ምክንያት ታፍነው የነበሩ ሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ዛሬ ባለንበት በ21 ኛው ክፍለ ዘመን በዲሞክራሲ መንግስት ምስረታ ፤ የግለሰቦችን ነፃነት የሚያከብር እና የህዝብን እኩልነት የሚገነዘብ መንግስት ሲኖር መልስ የሚያገኙ እንጂ አንድ ጠባብ ቡድን የሚያሽከረክራቸውን የየአካባቢውን ቋንቋ ተናጋሪ ልሂቃን ብቻ ወንበር ላይ በማስቀመጥ በማስቀመጥ በፌዴራሊዝም በመቀለድ (ፌዝራሊዝም በመመስረት) የሚሆን ነገር አይደለም፡፡
ወያኔ ለ25 ዓመታት ያለፉት ስርዓት በትግራይ ህዝብ ላይ የጭቋና ቀንበር ዘርግተው ነበር ሲል፤ አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ የነበረው ስርዓት የአማራ ህዝብ ወኪል አድርጎ ያቀርባል፡፡ ይህንንም ስብከቱን በየክልሎቹ ባቋቃማቸው ወኪሎቹ አማካኝነት ባለፉት የጭቋና ስርዓት እኩል ተጎጂ በነበረው የአማራ ህዝብ ላይ ጥፋት እንዲታወጅበት አድርጓል፡፡ የአማራ አርሶ አደር እና ጭቁን ማህበረሰብ ጉልበቱ እስኪዝል እና ላቡን አንጠፍጥፎ በኢትዮዮጵያዊነት ከሚኖርበት ቀየ እንዲፈናቀል እየተደረገ ይገኛል፡፡ ቡንዝልፎ
ወያኔ የተባለው ትግርኛ ተናጋሪ ገዢ መደብ ግን እራሱን ብቸኛ የትግራይ ህዝብ ወኪል አድርጎ በማቅረብ የትግራይ ገበሬ ለእኩይ አላማው በማሰለፍ፡ በደረግ ግፋዊ አመራር የተማረረን የአማራ ህዝብ የእርካብ መወጣጫ አድርገገጓ ለስልጣን በቅቶል፡፡ ወያኔ ደርግን በማሸነፍ እና 25 ዓመት እኩይ አላማውን እንዲያስፈፅም የተከፋፈሉት ኢትዮጵያዊያን ምቹ ሁኔታ የፈፈጠረለትን አጋጣሚ ወያኔ በመታበይ የህዝብ ድጋፍ ያለው አስመሰለው፡፡ የኦሮሞን ህዝብ ከአማራው ጋር ለማጋጨት እና የኢትዮጵያ ህዝብ አንጡራ ሃብት እየዘረፈ በመቶ አመት በስልጣን ለመቆየት እና ለመፈንጨት የቆመጠው የዘረኛው ወያኔ ቡድን የወያኔ ተላላኪና ቡችላዎችን እንደነ አባዱላ ፤ ሙክታር  ከኦሮሚያ በማስቀደም ከአማራዉም ድንበር የሚሸጠው ደመቀ፤ ካሳ ተክለብርሃን የመሳሰሉትን በማሰለፍ የቆመጠለት አላማ መክሸፍ አለበት፡፡የወያኔ አኖሌ የማን ውጤት እንደሆነ ታሪክ በቅርቡ ፍረርድ ይሰጣል፡፡ በህዘባዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴዎች  የፈሰሰው የወንድሞቻችን ደም በቅርቡ  የወያኔዎች መጨረሻ እንደጋዳፊ ስለሚሆን ፈሶ አይቀርም፡፡ ኦሮሞ እና አማራ ወንድማማች እና አንድ ህዝብ እንጂ  የወያኔ 25 ዓመት የደገሰላቸው እርስ በእርስ እልቂት ተቀልብሶ አሁን የደረሱበት የትብብር መንፈስ መቀጠል አለበት፡፡

ወያኔ በአንድ በኩል አገሪቱን ተቋጣጥሮ ኢኮኖሚዉን እንዳሻው እየመዘበረ በሌላ በኩል ደግሞ የትግራይ ሪፐፕሊክን የወደፊት ግዛት ማስፋፋት አቅድ እየተገበረ ይገኛል፡፡ የወልቃይት ጠገዴን እና ራያ እና አዘቦን ግዛት በጠመንጃ ወደራሱ ግዛት ካደረገ በኋላ ተከዜ ማዶ ያለ ግዛቱን ለማስፋፋት ተጨማሪ ወረዳዎችን በቅርብ ጊዜ በህዝባዊ ሪፈረንደም ለመጠቅለል እየቃዠ ያለ ገዢ መደብ ነው፡፡ የወልቃት የማንነት ጥያቄ ለ25 ዓመታት መስዎዕትነት የተከፈለበት ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ሁነኛ ምዕራፍ ላይ ደርሶል፡፡
ወያኔ ኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ስለሌለው በትግራይ ድርቅ ማግስት የደርግ መንግስተ በድርቅ የተጓዱ የትግራይ ገበሬን  ወደ ሌላ የኢትዮጵያ ግዛት ሲያሰፈር  በወቅቱ አማፂው የወያኔ ቡድን የትግራይን ህዝብ ከቀየው ተፈናቀለ ቢልም በድርቅ ለተጓዱት የተላከለትን እርዳታ ግን እታገለለታለሁ ለሚለው ህዝብ አንድም ሳያሸት መሳሪያ ታጥቋበታል፡፡ የጭቁን ገበሬዎች  ጥያቄን አንግቦ የተነሳው ወያኔ ዛሬም ከገባሬው ጋር እንደተቃቃረ ይገኛል፡፡

በትግራይ ህዝብ ስም እየማለ በተግባር ግን የትግራይን ህዝብ እንደህዝብ ከሚጎራበታቸው ወንድም ህዝብ ጋር ለማቃቃር እየሰራ ያለው ወያኔ/የትግራይ ነፃ አውጭ ቡድን ነው፡፡ ጦር ሰራዊቱን ፤ የሃገር ደህንነት መስሪየ ቤቱን፤ ቢሮክራሲዉን እና ኢንቨስትመንቱን አንድ አናሳ ቁጥር ካለው የኢትዮጵየያ ህዝብ አካል ከሆነው ከትግራይ የመጡ ፤ ክህሎቱ እና እዉቀቱ የሌላቸው እንደተቋጠጠሩት የአደባባይ ሀቅ ነው፡፡ ይህን ሀቅ የትግራይ ምሁራንም ሆነ ወጣትም በዝምታ ማለፋቸው ምን ይሆን፡፡
የትግራይ ምሁራን እና ወጣቶች ዛሬ ትግሬ እንደ አንድ ታታሪ ህዝብ በላቡ እና በጥረቱ የተሻለ ደረጃ ሊደርስ እና የተሸለ ህይወት ሊኖር የሚችለው በኢትዮጵያ አገራችን በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት ስንችል ነው፡፡ ይህ ስርዓት እውን ሲሆን ነው የትግራይ ህዝብ እውነተኛ ልጆች የሚፈጠሩት ፤ ትግሬም እንደ ህዝብ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ታሪክ በሌሎች ወገኖቹ የሚወደሰው፡፡  የትግራይ ነፃ አውጭ የቀድሞውን የደርግ መንግስት ስለ ወጋ እና ስላጣን ስለያዘ የትግራይ ህዝብ ብቻ መስዎዕትነት የከፈለ የሚመስላቸው የዎሆች፡ አለፍ ሲልም የትግራይ ህዝብ ብቻ ጀግና የሚመስላቸው የወያኔ ጠባብ ፖለቲካ ሰላባ የሆኑ የትግራይ ወጣቶች ማወቅ ያለባቸው  ሰው ሁሉ እኩል ነው የሚለው ሃቅ ብቻ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያዊያን እያካሄዱት ያሉት ህዝባዊ አመፃ የጋራ ቤታችንን ኢትዮጵያ ሁላችንንም በእኩልነት እንድታስተናግደን ያለመ፤ የኢትዮጵያ አንጡራ ሃብት ከስግብግብነት ወጥተን የጋራ ማድረግ ከቻል በቂ ነው፡፡ ህዝባዊi አመፃዉን የትግራይ ወንድሞቻችን እንዲደግፉት እና ደፍረው እንዲወጡ ጥሪየን አቀርባለሁ፡፡ኢትዮጵያ በመስዎዕት ልጆቾ በክብር ለዘላለም ትኖራለች፡፡