Followers

Wednesday, August 30, 2017

እንቦጭ ና ወያኔን ነቅለን የጣልን ለት!



እንቦጭን ከጣና ወያኔን ከአፍር ላይ ነቅለን የጣልን ለት፤
የባህርዳር ፈርጥሽ  የአፋር ገሞራ አለት፤
ታትሞ  ይቀራል   በአለም-አቀፍ መዝገብ  ይሆናል ቅርስ ውበት፤
መቼ ይጎልና አሳውም ከጣና በከል ወተቱ አፋር ቤት፤
ሕብረታችን ይታይ  አንዱ ለአንዱ ይድረስ ፤
ዋጋ ያስከፍላል መታገስ እኛ ዘንድ አስቲደርስ ፡፡

የማህበራዊ ልማት ልማት አጥኝዎች ጥናቶቻቸውን ተደራሽነት ለመጨመር የገጠሩን ማህበረሰብ አሳታፊ የሆነ የጥናት መንገድ (Participatory Rural Appraisal) መጠቀምን ይመክራሉ፡፡ እነዚህ የጥናት መንገዶች ተግባራዊ ማደረግ ለጥናታችን ግብዓት የሚሆነን መረጃ ማንበብና መጻፍ ከማይችለው (However, literacy and numeracy are quite different) የማህበረሰብ ክፍል ለጥናታችን ግብዐት የሚሆነንን መረጃ በአግባቡ ለማግኘት ያግዘናል፡፡ ለጥናታችን ግብዓት መረጃ ማግኘታችን ለጥናታችን የመፍትሄ አቅጣጫ ለማመላከት የራሱ ጉልህ አስተዎጽኦ አለው፡፡
የገጠሩን ማህበረሰብ አሳታፊ የሆነ የጥናት መንገድ (Participatory Rural Appraisal) ውስጥ ለወሳኝ ክስተቶች መረጃ ማግኛ ዘዴ (Timeline/Historical Mapping) አንዱ ሲሆን የማህበራዊ ልማት ልማት አጥኝዎች በጥናታቸው አካባቢ ወደ ሆላ ተጉዘው ምን ምን ክስተቶች እንደነበሩ የጥናቱ ተሳታፊዎችን የሚጠይቁበት መንገድ ነው፡፡
ከላየ ያለውን ሃተታ ያነሳሁት በአፋር ክልል ላይ ስለተከሰተው “PROSOPIS” የተባለ አረም የማህበራዊ ልማት  አጥኝዎች የተቸገሩበትን ጉዳይ ስላየሁ ነው፡፡ ይህ ዓረም ወያኔ እየተባለ በአፋር ነዎሪዎች ዘንድ የሚታወቅ ቢሆንም አንዳንድ የማህበራዊ ልማት አጥኝዎች የጥናት ወረቀቶች ስመለከት ደርጊ እያሉ በጥናታዊ ፅሁፋቸው ገልጠውታል፡፡ በአፋር የሚገኘው ወያኔ የተባለው አረም ከወያኔ ጋር አብሮ መጣ ብለው ስለሚያምኑ እና ለ26 ዓመት በአፋር የሚገኝ ሆኖ በአርብቶ አደሩ የግጦሽ መሬት ላይ ወረራ በማካሄድ ለአርብቶ አደሩ የራስ ምታት ሆኖበታል፡፡ እንቦጭ በጣና ስንት ዓመት ሆኖት ይሆን?

ብዙ ብር ወጥቶባቸው ጥናት የምታደርጉ ተቋማት ወደ እውነታው ተመለሱ፡፡ ጥናት ማድረግ ሌላ ፤ ፖለቲካ ሌላ ነው የእኔ መልዕክት፡፡ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ደግሞ በእንግሊዘኛ መጠቀም መርጠዎል (http://www.ena.gov.et/index.php/economy/item/11520-2017-02-05-17-32-42)፡፡ ምናልባት የመገናኛ ብዙሃን ሪፎርም እየተዘጋጀ ነው ተብሎ የተራገበለት ይኸን ይቀርፍ ይሆን? አብረን እናያለን፡፡ አብራሃም ለቤዛ

Friday, August 11, 2017

ግብር ለምን ዓላማ?



በኢትዮጵያችን ገቢ ለልማት ከቴሌቪዢን ፕሮግራም ባለፈ በኢትዮጵያ ለልማት ይውላል ወይ ነው ቁልፋ ጥያቄ፡፡ በብድር ፤ በእርዳታ ፤ ኢትዮጵያዊያን ለቤተሰቧቻቸው ከስደት አገር የሚልኩት ገንዘብ እንዲሁም መንግስት የሚሰበስበው ግብር (የአገር ውስጥ ገቢ) የገቢ ምንጮች ናቸው፡፡ ገቢ ለልማት ብንልም ቅሉ ገቢው ልማት ላይ መዋል አለመዋሉን መቋጣጠር የሚችል የማህበረሰብ ተሳትፎ መፍጠር አልቻልንም፡፡ እኔ አውቅልሀለሁ የሚል ገዢ ፓርቲ ያልሁህን አምጣ የማለት የሞራልም የህግም መብት የለውም፡፡ አሳታፊ እና ተጠያቂነት ባለበት ስርዓት ግን ዜጓች ግብር መክፈል የውዴታ ግዴታቸው ነው፡፡ የሚወዶትን አገራቸው ማልማት፡፡ ቃልና ተግባር ለየቅል ሆነ እንጂ፡፡ ግብር አስፈፃሚው አካል ሙሠኛ ከሆነ እንዴት ግብር ከፋዩ ሀገርህን ስለምትወድ ብለን እናሳምነው? የተጣለብኝ ግብ ፍትሀዊ አይደለም ሲል የይግባኝ ስርዓት ከሌለን ወይንም ሁሉንም ነጋዴ በእኩል አይን የምናይበት ፍትሀዊ አሰራር ግብር ሰብሳቢው አካል ላይ ከሌለ እንዴት ግብር መሠብሠብ ይቻላል፡፡ ኢትዮጵያ የግብር ተደራሽነት ከሌሎች አፍሪካ አገሮች አንፃር ሰፊ መሠረት እንደሌለው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ለዚህም ነው በየአመቱ የሚታወጀው በጀት 50% በላይ በብድርና ዕርዳታ ይሸፈናል እየተባለ ቃል የሚገባው፡፡ ነገር ግን በዕርዳታ የሚመጣውም ገንዘብ ሆነ ብዙ ዳፋ ለትውልድ እያስተላለፍንለት ያለው ብድር በሙስና ይባክናል፡፡ የኦዲት ባለሙያዎች ምስጋና ይግባቸውና በሪፖርታቸው ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየገለፁት ነው፡፡ የግብር መሠረት ለማስፋት አሳታፊና ፍትሀዊ ስርዓት ያስፈልገናል፡፡ በግብር የተማረረው ዜጋም እንደዚህ ነው ብሷቱን በስነ-ቃል እየገለፀ የመጣነው፡፡
******ዓፄ ቴዎድሮስ ጎጃ ዘምተው ሕዝቡን በዘረፉበት ጊዜ ጉዳት የደረሰባት አንዲት ሴት እንዲህ ብላ አለቀሰች፡፡
ልብሴንም ገፈፈው፤ ለበሰው እርዘኛ፤
በሬየንም ነዳው አረደው ነፍጠኛ፤
እህሌን ዘረፈው በላው ቀለብተኛ፤
ንጉሥ የቀረዎ ጥቂት አማርኛ፣
 ምነው ሆድ አይዘርፉ አርፌ እንድተኛ፡፡

*****
ራስ ኃይሉ በዘመኑ የጎጃምን ሕዝብ (የኔ ቢጤ ደሀን ለማኙን ሳይቀር) “ግብር ክፈልእያለ በአስጨነቀበት ወቅት ሕዝቡ እንዲህ ብሎ ስሜቱን ገለጠ፡፡
ጎመኑን ቀርድጄ ጥሬውን በላሁት፣
 እንዳላበስለውም የጭሱን ፈራሁት፡፡
ራስ ኃይሉ ጭስ የሚጨስባትን እያንዳንዷን ጎጆ እያስቆጠሩ፣ ግብር ያስከፍሉ ስለነበር በጎጃም ሚስት ያገቡ ወጣቶች ጎጆ አይወጡም ነበር፤ ትልቁ ቤት እየተዘረጠጠ በታዛ ውስጥ ይኖሩ እንደነበር አባቶቻችን ይናገራሉ፡፡
አሁንስ እንዲህ ብለን ብንቃኝ አይቻል ይሆን?

ገቢ ለልማት መሆኑን አውቃለሁ፤
ኢትዮጵያ አገሬንም በጣም እወዳለሁ፤
የቄሳርን ለቄሳር ቅዱስ ቃሉ ይላል፤
ኮረጆ ገልብጠህ ድምጤ የሰረቅከኝ በብር ማን ያምንካል፡፡