Followers

Sunday, October 15, 2023

ኤርትራና ሲንጋፖር -አብራሃም ለቤዛ

 

 

ኤርትራና ሲንጋፖር
አብራሃም ለቤዛ
>><<>><<>><<>><<>><<>><<>><<>><<>><<>><<>>><<>><<>><<>><<>><<>><<
ኤርትራና ሲንጋፖር
አብራሃም ለቤዛ

ኤርትራ ከሲንጋፖር ጋር ለመተረክ የፈለግኩት ከሰሞኑን የኤርትራ የተባበሩት መንግስታት ተቀማጭ አማባሳደር ከሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስተር  Mr. Yap Ong Heng ጋር ተገናኙና ተወያዩ የሚል ዜና ነው፡፡  ነገር ነገር ያነሳዎል እንዲሉ ለመተረክ የፈለግኩት ስለሁቱ አገሮች ግንኙነት ሳይሆን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር እንሆናለን ይል ስለነበረው የኤርትራዊያን ቅዠት ነው፡፡

የኤርትራ መንግስት ከኢትዮጵ ለመገንጠል በሚያደርገው ጥድፈት ዋዜማ ኤርትራን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር እናደርጋታል ይል ነበር፡፡  የየደቡብ ምስራቅ ኤሺያ አገሮች በአጭር ጊዜ ከድህነት ስለወጡ ለብዙ የአፍሪካ አገሮች መቅኛ ነበሩ፡፡  ፈጣን እድገትና ልማት ግን ትክክለኛ  የፖሊሲ አቅጣጫ በመያዝ የሚመጣ እንጂ በማለም ብቻ የሚሆን አይደለም፡፡  የኤርትራዊን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር የመሆን ምኞት የመጣው ራሳቸውን ከሌላው ሀባሻ የኢትዮጵ ህዝብ እንዲሁም ከትግሬ ወንድሞቻቸው ለይተው ማየታቸው ነው፡፡ የ60 ዓመት የጣሊያን ቅኝ ገዢ ፖሊሲ በኤርትራዊያን ላይ ይኸ አስተሳሰብ እንዲጫን አድረጎል፡፡ ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ “Ethiopia and Eritrea- The Federal Experience”  በሚለው ጥናታዊ ፅሁፋቸው ኤርትራዊያን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዳግም የሄዱበት መንገድ እኛ የተለየን ነን ፤ ከሃበሻ እኛ የሰለጠንን ነን፤ እኛ ከተገነጠልን በፍጥነት እንበለፅጋለን የሚለው አስተሳሰብ ስለሰረፀባቸው ነው ይላል፡፡

የሆነው ግን ኤርትራ የአፍሪካ ሲንጋፖር ሳይሆን የአፍሪካ ሰሜን ኮርያ ሆነ፡፡ የሃበሻ ምቀኝነት እንዲሉ ለዚህ ደግሞ የወያኔ ኢተዮጵያ ኤርትራን በማሳጣት ትልቅ አስተዋፅኦ አድርጋለች፡፡

የደቡብ ምስራቅ ኤሽ አገሮች ሲንጋፖር ፤ ማሌዥያ፤ ቬትናም፡ታይላድ ፤ኢንዶኔዢያና ፊሊፒንስ ሲሆኑ ፤ በአጭር ጊዜ ከድህነት በመውጣታቸው ምክንያትም የኤሽያ ታይገር የሚል የዳቦ ስም ወጥቶላቸዋል፡፡  የወያኔዎ ኢትዮጵያ ልማታዊ መንግስትን በመከተል የደቡብ ምስራቅ ኤሽያ አገሮች መንገድ እከተላለሁ ብትልም፤  ነገር ግን የኢትዮጵያ ፖሊሲ በጎሳ ፖለቲካ ፤ የጋራ መግባባት የሌለው ፖለቲካ ሃይል እና በሙስና የተጨማለቀ ፖለቲካ ሃይል የተተበተ ስለሆነ የደቡብ ምስራቅ ኤሽያ አገሮችን ፈለግ መከተል አልቻለችም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለራሷ የአፍሪካ ላይዮን የሚል የዳቦ ስም አውጥታለች፡፡ ለከታታይ 14 ዓመት (2005-2019)  በሁለት ዲጂት ያደገ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚል የተለመደ የወያኔዎች የአፍ ማሞሻ ጥቅስ ነበር፡፡

ፅንፈኛው ጃ-War  መሃመድ   የኦሮሞ ፖለቲከኛም በሲንጋፖር ኢኮኖሚ እምርታ እንደሚማረክና ሲንጋፖር እየተማረ

የሲንጋፖርን እድገት እናዳጠናዉም በተደጋጋሚ ይገልፃል፡፡ ችግሩ የሲንጋፖርና የደቡብ ምስራቅ ኤሽያ አገሮች ሲንጋፖር አገሮች መመንደግ ሳይሆን እነሱ የሄዱበትን  እኛ እንዳንሄድበት  ራሳችንን አድርገናል፡፡ የእኛ መንገድ ማለት በህገመንግስታችንም ሆነ በኢኮኖሚ ፖሊሲያችን ኢትዮጵያዊነት በዜጋነት እንዲደራጁ አንፈቅድም፡፡  የብሄር ፖለቲካ ይዘን እንደ ዝንጀሮ መንጋ ባለች ሃብት (ክምር) ላይ ሰፍረን መበዝበዝ እንጂ ምርታማነትና ዕድገትን አናመጣም፡፡

ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ እንዲሉ የአፍሪካ ፖለቲከኞች ፊት ለፊት ያገጠጠ ፖለቲካ ችግራቸውን ከመጋፈጥ ይልቅ የጦስ ዶሮ መፈለግ ይዘዎል፡፡ አዎ ላላማደጋችን ወደብ-አልባ አገር መሆናችን ትለቅ አስተዎፅኦ አለው ነገር ግን አሁን ያለንበት ተጨባጭ ሁኔታ ሌላ የበለጠ አሳሳቢ ጉዳያችንን መፍታት አልቻልንም፡፡ አገርን ሰላም ማድረግ መንግስት አልቻለም፤ ዜጎች በሰላም ወጥተው መግባት አልቻሉም፡፡

ብልፅግና መራሹ ፤ የኦሮሞ ፅንፈኞች ከዚህ መማር ቢችሉ ኢትየጵያዊያንን በአንድ ማስተባበር አለባቸው፡፡ ብቻቸውን ግን ቀይ ባህር ፤ ህንድ ውቅያኖስ የሚሉት አያዋጣውም፡፡ ሻብያና ኦነግ ከ30 ዓመት በፊት በአንድ ሰርተዎል ፤ አሁን ደግሞ አንዱ የጣለውን መንገድ አንዱ እያነሳ ባለህበት እርገጥ ሆኖል፡፡