Followers

Monday, October 11, 2021

ያልተዘመረለቱ ጸረ ፋሽስት ኢትዮጵያዊ አርበኛ:– ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ! አቻምየለህ ታምሩ

 በሰው ልጅ ሕይዎት ውስጥ ትልቁ ጥያቄ ስንት ዘመን ኖርን የሚለው ሳይሆን ረጅሙንም ሆነ አጭሩን ዕድሜ እንዴት ኖርነው የሚለው እንደሆነ አብዛኛዎቹ አሳቢዎች ይስማማሉ። የምንኖርባት ፕላኔት ለቁጥር የሚበዙ በርካታ ወጣት ጀግኖች ያፈራች፤ በደማቸው አዲስ ታሪክ የጻፉና የነጻነት ፋኖ የለኮሱ የአንድነት ቀንዲል ሆነው በታሪክ ቅብብሎሽ ሂደት በብዙዎቻች ልብ ውስጥ ታትመው የሚኖሩ ሰዎች ያለፉባት ምድር ናት።

አገራችን ኢትዮጵያ ለእናት አገራቸው ቀድመው የደረሱ፣ አንተ በመባያ የልጅ እድሜያቸው አንቱ የሚያሰኝ ድንቅ ስራ የሰሩ፤ ላገራቸው ሩቅ አሳቢ ሆነው የወጣትነት ትኩረታቸው ብዙ ዘመን እንደተጠራቀመ የሽምግልና ምክር ለዘመናት የሚያስተጋባ ተግባር የነበራቸው ጀግኖች ነበሯት። በዛሬው ጽሑፋችን አገራችን ኢትዮጵያ ከነበሯት ከራሳቸው በላይ ላገራቸው የሚያስቡ፤ ምክራቸው አገር የሚያውል ትላልቆች መካከል ቀዳሚው የሆኑትን የወጣቱን የጸረ ፋሽስት ጥሊያን አርበኛ የሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብን ታሪክ እናወሳለን።
በዚህ የሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብን ታሪክ በዳሰስንበት ጽሁፍ የተጠቀምናቸው የታሪክ ምንጮቻችን ታደሰ ሜጫ በ1942 ዓ.ም. «ጥቁር አንበሳ፣በምዕራብ ፣ኢትዮጵያ» በሚል ያሳተሙት መጽሐፍ፤ ሐዲስ ዓለማየሁ በ1985 ዓ.ም. «ትዝታ» በሚል ያሰናዱት ግለ ታሪክ፣ አቶ ተፈራ ይኼይስ በ1952 ዓ.ም. «የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጦር ትምህርት ቤት ብሩራዊ ኢዮቤልዩ» በሚል ያዘጋጁት መጽሐፍና ጀኔራል ነጋ ተገኝ በ1985 ዓ.ም. «የኢትዮጵያውያን የረዥም ዘመናት ትግልና የዘመናዊ ሰራዊት አመሠራረት 1855-1974» በሚል የጻፉት መጽሐፍቶች ናቸው።
በላይ ኃይለ አብ ወደ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የጦር ትምህርት ቤት ከመግባቱ በፊት በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የፈረንሳይኛ ትምህርት ተምሮ በእውቀት ከጎለመሰ በኋላ ፍላጎቱ በወታደርነት ግልጋሎት ለውድ አገሩና ለኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ክብር የሚገባውን መስራት በመሆኑ ወደ ገነት ጦር ትምህርት ቤት በመግባት የጦር ትምህርት ተምሯል።
በላይ ኃይለ አብ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጦር ትምህርት ቤት ገብቶ ከተማረና አስፈላጊውን የመኮነንትን ውድድር ከጨረስ በኋላ በመልካም ጠባይና ችሎታው እንዲሁም በጦር ትምህርት ቤት ባሳየው መልካም አርአያ ተግባሩ የተዋጣለበት መኮንን በመሆኑ በሌተናት ኮሎኔልነት ማዕረግ በቅቶ ተመርቋል። በ1928 ዓ.ም. ጠላት ሀገራችንን ለመውረር በመጣ ጊዜ ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ አገሩን ለማገልገል ለገባበት ቆራጥ መንፈስ ታጥቆ በመነሳት የጠላት ጦር ድል እያደረገ ወደ አዲስ አበባ በመቃረቡ አንድ ሻለቃ ጦር እየመራ ወደ ጣርማ በር አዝምቶ ለሚቀጥለው ሲጠባበቅ ከድል በኋላ ለወደፊት የአርበኝነት ሥራውን ለመቀጠል ሲል በጠቅላይ ሠፈሩ የሚገኘውን ጦር አሳብሮ ጠላት ወደ አልደረሰበት ለቀምት ሄደ። ጦሩም ከገነት ተነስቶ ወደ ምዕራብ በሚጓዝበት ጊዜ ለጠላት ተሰብኮ የነበረውና አላዋቂውም ባላገር አላሳልፍም በማለት ከባድ ጦርነት በየመንገዱ ቢያደርግባቸውም እነ ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ግን ከአዲስ አበባ ተነስተው ለቀምት የደረሱት የራቀውን በመምከር፤ የቀረበውን በማስረዳት በኃይልም ለመጣ መልስ በመስጠት ነበር።
ለቀምት እንደገቡ የአውራጃው ገዢ የነበሩት ደጃዝማች ሀብተማርያም እስከ መጨረሻው በአርበኛነት ለመቆየት እንዲቆርጡና ለመተባበር ያበቋቸው የዚሁ መኮንን ፍጹም አስረጁነት ስለማረካቸው ነበር። ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ በአዛዥነቱ በምስጉንነቱ በቀልጣፋነቱ ወታደሩ የፍቅር ዓይን ጥሎበት ስለነበረ የጥቁር አንበሳ ጦር በምዕራብ ኢትዮጵያ ሲቋቋም በምርጫ ድልድል የጥቁር አንበሳ ጠቅላይ የጦር አዛዥና አሰልጣኝ ሆነ። እንደሚታወቀው የጥቁር አንበሳ ጦር በዳግም ጥሊያን ወረራ ወቅት ሁሉም ሀገሩን ሊታደግ መከራውን ሲያይ በነበረበት ዘመን የሆለታ ገነት የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የጦር ትምህርት ቤት ምሩቃን የነበሩ የጦር መኮንኖች 400 ያህል ሆነው መቀመጫውን ነቀምት አድርጎ የተመሰረተ ድርጅት ነው።
የጥቁር አንበሳ የጦር ድርጅት ፕሬዝደንት የኢትዮጵያ የመጀመሪያው የእንስሳት ሕክም ባለሞያው ዶክተር አለመ ወርቅ በየነ ሲሆን የጦሩ አዛዥና አሰልጣኝ ደግሞ ባለታሪካችን ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ነበር። ከሁለቱ ታዋቂ አርበኞች በተጨማሪ ድርጅቱ በአርበኛነት የከንቲባ ገብሩ ደስታ መላ ቤተሰብን በሙሉ ያቀፈ ሲሆን በአመራርነት ደግሞ 25 ስመጥር የጦር መኮንኖች እና ታዋቂ ሲቪሎች ነበሩ። የጦር ማህበሩ አላማ ጠላትን መፈናፈኛ በማሳጣት ለእናት አገር መሞት ብሎም ወጣቶችን ለሀገራቸው ዘብ እንዲቆሙ መቀስቀስ ነበር። ለዚህም አለማ ይሆን ዘንድ የሚከተለውን ቀስቃሽ የድርጅቱን መዝሙር በየቦታው ይበትኑ ነበር፤
በለው፤ በለው!
አትለውም ወይ አትለውም ወይ?
ጥቁር አንበሳ አይደለህም ወይ?
ኸረ በለው፤ ኸረ በለው! በለው! በለው!
አትለውም ወይ አትለውም ወይ?
ጥቁር አንበሳ አይደለህም ወይ?
ኸረ በለው፤ ኸረ በለው!
አትለውም ወይ አትለውም ወይ!
የጠቅል ሎሌ አይደለህም ወይ?
በለው፤ በለው!
አትለውም ወይ አትለውም ወይ!
ያድዋ ጀግኖች ቅርስ አይደለህም ወይ?
ኸረ በለው፤ ኸረ በለው!
አትለውም ወይ አትለውም ወይ!
ለዙህ ላታላይ ትሠጋለህ ወይ?
ኸረ በለው፤ ኸረ በለው!
አትለውም ወይ አትለውም ወይ!
ጥንታዊ ጀግና አይደለህም ወይ?
ይህን መዝሙር በድምጽና በሙዚቃ የሚያሰሙት ይልማ መንገሻ የሚባሉ አርበኛ ነበሩ። ኋላም ይህ መዝሙር ወደ ካርቱም ተሰዶ ቆይቶ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በድል አድራጊነት ወደ መናገሻቸው ሲገቡ ለጉዞው ፊታውራሪ ሆኖ አብሮ እየገሰገሰ አርበኞች በሰልፍ እየዘመሩት ቤተ መንግሥት ድረስ ደርሷል።
ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ በለቀምት የወታደር አሰልጣኝነቱንና የአዛዥነቱን ኃላፊነት ከተሰጠው በኋላ በኅብረት የታጠቀው ጦር መልካም አደፋፋሪና መሪ በማግኘቱ፤ በሥልጣኔም በጦር ታክቲክም ይበልጥ እየሰፋ በመሄዱ በደረሰበት ሥፍራ ሁሉ ጦሩ ጥሩ የጀግና ስም ማትረፍ ችሏል። ከድርጅቱ ቀስቃሽ መዝሙር በተጨማሪ ጥቁር አንበሳ የጀግና ስም ማትረፍ የቻለው ድርጅቱ ጠንካራ የመተዳደሪያ ደንብና ሕግ ስለነበረው ነበር።
ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ የሀገር ፍቅር ስሜቱ ውስጡን ያቃጥለው ነበርና በየጊዜው ጦሩን የጀግኖችን አባቶቻችንን ክብር ሳናበላሽ ለጠላት ተዋርደን ሳንገዛ የንጉሠ ነገሥቱን አደራ ሳናጠፋ እስከ መጨረሻው ተጋፍጠን መዋጋት አለብን እያለ የጀግኖችን ወኔ የሚቀሰቅስ ድምፅ እያሰማ ይሰብክ ነበር። በ1928 ዓመት ምሕረት ጦሩ ለቀምት ላይ እንዳለ ሦስት የጠላት አውሮፕላኖች አንዣበው በቦንያ ባረፉ ጊዜ፤ ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ የጠላትን ጦር ተመልክተን እንዴት ልናልፋቸው እንችላለን በማለት ጉዳዩ በኮሚቴ ተጠንቶ ከተወሰነ በኋላ አውሮፕላኖቹን ለማቃጠል ቁርጥ አሳብ እንዲደረግ በጽኑ የመከረ ቆራጥ መኮንን ነው።
በሌላም በኩል የአውሮፕላኖቹ ጥፋት የበለጠ ጉዳት አስከትሎ እኛንም ሆነ ሕዝቡን ይጎዳን ይሆናል ተብሎ በተገመተ ጊዜ መኮንኑ አስቀድመን ተፈልገን ከምንጠፋ እኛ አጥፍተን መጥፋት አለብን በማለት ለኮምቴው አደፋፍሮ ከገለጸ በኋላ በድፍረቱ ተዋጊውን ጦር አስከትሎ አውሮፕላኖቹ ወደ አረፉበት ሥፍራ ጉዞውን አመራ። ከዚያም ስለአጠቃቁ ዘዴና ፕላን እየሰጡ ከተጠጉ በኋላ በ12 ሰዓት ላይ ሲሆን ለግጥሚያው ትእዛዝ የሰጠ ነው። ጠላት የመትረየስና የጠመንጃ እሮምታ ሲተኮስባቸው ተዋጊው የጥቁር አንበሳም የተኩስ መልስ በመስጠቱ ሦስቱም አውሮፕላኖች ሲቃጠሉ አስር የሚሆኑ ከፍተኛ የፋሽስት ጦር መኮንኖች አብረው ሲቃጠሉ የተሳካውን ድንቅ ኦፕሬዥን የመራው ጀግናው ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ነበር።
መኮንኑ የሰጠው ትእዛዝ በመልካም ተከናውኖ በድል አድራጊነት ሲመለስ የጠላት ባንዲራ ከአውሮፕላኑ ውስጥ ተማርኮ ስለነበረ ከፈረሱ ጭራ ላይ አስሮ መሬት ለመሬት እየጎተተ ወደ ጠቅላይ ጦር ሠፈሩ ተመለሰ። በአዲስ አበባ እስከ ለቀምት በነበረው ዘመቻም ሆነ በዚህ ዕለት ባደረገው ሞያ መላው ጦሩ ስለአቀፈውና ስለወደደው ታዛዥነቱን ከልብ አደረገ። በዚህ ጊዜ ነበር ታዋቂው አርበኛና ባለ ቅኔ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ የጦሩን ሞራል ከፍ ለማድረግ
እናት ኢትዮጵያ ውዲቱ ውዲቱ፣
በሶስቱ ቀለማት የተሸለምሽቱ፣
ላንች የማይረዳ ሳለ በሕይወቱ፣
በረከትሽ ይንሣው እስከ ዕለተ ሞቱ።
ሲሉ የገጠሙና ሕዝቡን ለነለጠ ተጋድሎ ያነሳሱት።
ከተሳካው የቦንያ ኦፕሬሽን በኋላ ሌተናት ኮሎኔል በላይ የጠላት ወደ አውራጃው መምጣትን በመረጃ እየተከታተለ ጦሩ በአደጋ እንዳይጎዳበት ዘዴና ፕላን በማውጣትና ሐሳቡንም ለኮሚቴው በሚያቀርብበት ጊዜ ትክለኛና የማያወላውል መኮንን መሆኑን በበለጠ ማስመስከር ቻለ።
ከቆይታ በኋላ የጦሩ ለቀምት በመቆየት በአገረ ገዢው በተጠላ ጊዜና እንዲለቁላቸውም ተጠይቀው ስለነበረ በእምቢታ ቢቆዩ ጦሩ አደጋ ላይ ሳይወድቅ አይቀርም በማለት ወደ ጎሬ ሄዶ በተሻለ ሁኔታ ለመቋቋም ሲታሰብ መኮንኑ ትክክለኛ ሐሳብ መሆኑን ያስረዳ ነበር። ከልዑም ራስ እምሩ ጋር በመገናኘት ሐሳብ ለሐሳብ ሲለዋወጡ ልዑልነታቸው የጎሬውን ጦር መፈታት አይነት ለጥሊያን እጅ ለመስጠትና ወደ ስደት ለመሄድ ሲያስቡ መኮንኑ ግን ወደ ወለጋ ተመልሶ ጠላትን ተከትሎ መውጋት የተሻለ ነው ሲል ክርክር አቅርቦ የሌሎቹን ልብ ለመማረክ በመቻሉ ወደ ወለጋ ያለውን ጉዞ በማደፋፈር ጉይ ላይ የሚደረገውን ከባድ ጦርነት ድል ለመንሳት የሚረዳውን የውጊያ ስልት መስጠት ጀመረ።
ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ የአዛዥነቱን ሥልጣን በማጠንከር በየቦታው አዋግቶና ተዋግቶ ለገጠመው ችግር መካች ሆኖ የጦሩን መንፈስ ከማበረታታት ያልተመለሰ ጀግና ነበር።
እንዲሁም የጦር መስመሩ ወደ ጂማ እንዲዛወር ተቆርጦ በሚጓዝበት ጊዜ የሀገሬውን ንብረትና ሀብት እንዳይዘረፍ ወይንም እንዳይበላሽ ከፍ ያለ መቆጣጠርና ሥነ ሥርዓትም እንዲከበር ጥብቅ ትእዛዝ በመስጠት በትክክል የመራ ነው። ጦሩም ጉማ በደረሰ ጊዜ ጅማ ድረስ ሄዶ ጠላትን ለመውጋት ለቀረበው ሐሳብ አንደኛው ዘዴ ሰጭ ነበረ። በየመንገዱ በደረሰበት አደጋ ተስፋ እንዳይቆርጥ የጦርነቱም መከራ እያንዳያንደገግፈው ሲያበረታታ የቆየ ነው። ለቀምት እንደገቡ የነበራቸው ብዛት 400 መሆኑን እንዳስረዳነው በየጊዜው በደረሰው አደጋ በጠቅላላው 250 ሰዎች ያህል ሲሞቱ ምንም ቅር ሳይላቸው እነርሱም ተራቸውን ለመቀበል የሚሽቀዳደሙት የዚህ መኮንን ቆራጥ አዛዥነት በሚሰጠው ጽኑ እምነት ነበር።
ልበ ሙሉ የሆነው መኮንን ጦሩን እያደፋፈረና እያጽናና ጎጀብ ሲደርስ ከወዳጅ ጠላት ወጥመድ ሲገባ ቆራጡ መኮንን ከመማረኩ በፊት ተታኩሶ ከጠላት ክበብ ውስጥ የቻለ እንዲያመልጥ ቆርጦ ነበረ፤ ነገር ግን የመጨረሻው ሐሳብ ተማጽነው የተጠጓቸው ሕጻናትና ሽማግሌዎች አናስፈጅም በማለት መማረክ ስለተመረጠ መኮንኑ በጠላት እጂ ቢወድቅም ልቡን ለጠላት ሳይሰጥ በምርኮ እንደተጉላላ ጂማ ድረስ ሲመጣ ከዚያም በስቃይ አዲስ አበባ ታስሮ ደረሰ።
በዚህ መሠረት አዲስ አበባ እንደገባ በከባድ ተግሣጽ ይቅርታ ተደርጎላቸው ለሞታቸው አጋጣሚ ጊዜ ይጠበቅላቸው ስለ ነበረ፡ ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ለጊዜው ሕይወታቸው ከሞት ቢተርፍም በማናቸውም ጊዜ እንደሚገድሉት ያውቅ ነበረና ከጠላት ከበባ ውስጥ ወጥቶ በአርበኛነት የሚሰራበትን ጊዜ ሲጠባበቅ በግራዚያኒ ላይ የቦንብ አደጋ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. በተደረገው ምክንያት ጠላት የፍላጎቱ መፈጸሚያ ስላገኘ ይዘው አስረውት የአደጋው ተባባሪ ነህ በማለት ሲገድሉት ከብዙ መኳንንንቶችና መኮንኖች ጋር በእግር ብረት ታሰረ።
ወንጀል ሰርተሃል በተባለበት ጥፋት ምርመራ በሚደረግበት ጊዜ ብዙዎቹ እየተጠሩ ከባድ ስቃይና የሞት ፍርድም ሲፈጸምባቸው ቆይቶ የሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ተራ ሲደርስ ተጠርቶ በአንድ ሃምሳ አለቃ ተይዞ ወደ ምርመራው ሥፍራ እንዲሄድ ቢጠየቅ፣ መሞቱን ያረጋገጠው ቆራጡ መኮንን «እኔ ሌተናት ኮሎኔሉ በአንድ የበታች ሹም ታጅቤ ለመሄድ ክብሬ አይፈቅድልኝም፤ ይህንን አድርጌ ያስተማረችኝን እናት አገሬን ሊያዋርዷት በመጡ ጠላቶቿ ፊት አላዋርድም፤ ቢፈልግ አዛዡ ይምጣና እሄዳለሁ» ሲል መለሰለት። የሃምሳ አለቃው ወደ ምርመራው ሹም ሄዶ «በአንድ አነስተኛ ሹም ተይዤ አልመጣም» ማለቱን ለበላይ አለቃው አመለከተ።
በዚህ ጊዜ ሌላ ሻምበል ይዞት እንዲመጣ ተደርጎ ሻምበሉም ትእዛዙን ነግሮ እንዲከተለው ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብን ቢጠይቀው «ክብሬ አንተን ከመሰለ ጋር ለመሄድ አይፈቅድልኝምና እምቢ» ሲል በድጋሜ ገለጸ። ከዚህ በኋላ ሌላ አንድ ኮሎኔል ቢላክበት «ካንተ ጋር ለመሄድ ቅር አይለኝም» ብሎ በመከተሉ አጃቢውም መኮንን የቆራጡን መኮንን ኩሩ መንፈስ አድንቆ የሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብን አክብሮት በመፈጸም በቀኝ በኩል ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ አጃቢው በግራ በኩል ሆነው ወደ ምርመራው ቦታ ደረሱ።
በዚህ ወቅት ሌተናት ኮሎኔል በላይ የእምነት ክህደት ቃሉን እንዲሰጥ ሲጠየቅ ያለፍርሃትና ያለ ድንጋጤ «አገሬን ልወሩ የመጡ ብዙ ፋሽስት ጥሊያኖችን በማስጣቴ ደስታዬ ወሰን የለውም፤ ለሃገሬ፣ ለባንዲራዬና ለንጉሠ ነገሥቴ ስል የመጣውን አጥቂ ለመመከትም ሆነ ለማጥፋት የገባሁበትን የወታደርነት ቃልጊካድንና የኢትዮጵያዊነቴን ግዴታ ፈጽሜያለሁ» ሲል ተናገረ። ፋሽስቶቹም ይህንን መልስ በሰሙ ጊዜ የሌተናት ኮሎኔል በላይ ቆራጥ ወታደርና ጀግና ኢትዮጵያዊ መሆኑን ስላስገመተ ለወደፊት ለፋስት መንግሥት የማይገዛ አደገኛ እንደሆነ በመረዳት የሞት ቅጣት እንዲቀበል ፈረዱበት። የሞት ቅጣቱንም መጀመሪያ ወደ ወሎ ጠቅላይ ግዛት ወስደው ቦሩ ሜዳ ላይ አቶ ኃይለ አብ አባቱ ባሉበት ስፍራ ይኸውልህ ዓመጸኛ ልጅህን ተሰናበተው፤ ሊገደል ነው ብለው በአውሮላን ወደ ወለጋ በቦንያ ወስደው ከነሕይወቱ ከአውሮፕላን ውስጥ አውጥተው ወርውረው ገደሉት።
በስሩ ባሉ ወታደሮች ዘንድ በመልኩ የቀይ ዳማ፣ ቁመቱ አጠር ያለ፣ በአለባበሱና በአረማመዱ ቀልጣፋነት ያለው፣ንግግሩ የጣፈጠና ጦሩ በሙሉ የፍቅር አይን የጣለበት በሚል ይገለጽ የነበረው ጀግናው ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ለአገሩ የሚገባውን አድርጎ የሞት ጽዋን በፍቃዱ ለአገሩ ሲል ጨለጠ። በለቀምት የወታደር አሠልጣኝነትና የጠቅላይ አዛዥነት ኃለፊነት ከተሰጠው ጊዜ ጀምሮ ጦሩን በሥልጣኔ ከማራመዱ በላይ «ስለ አገራችን ነጻነትና እለንጉሠ ነገሥታችን ፍቅር ብንሞት በክብር እንወዳለን። ይህችን ነጻነት አባቶቻችን በአጥንታቸው መሥርተው በደማቸው ዋጅተው በአደራ ስላስረከቡን አደራችንን ሳናጠፋ እንደጠበቅን እንሞታለን እንጂ እኛ ለጠላት ተዋርደን የጅግናይቱን እናታችንን ክብር አናዋርድም» እንዳለው ሰማዕት ለመሆን በቃ።
ጀግናው ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ በጉዞ ጊዜ በፈረስ ሆኖ ዘወትር የሚሄደው ከግንባር ቀመድ ጦር ጋር ነበር። እንዲሁም ጦርነት በተጀመረ ጊዜ ሽጉጡን መዝዞ ከወታደር ፊት ፊት እየሮጠ የውጊያውን ጉዳይ ያከናውን ነበር እንጂ እንደጠቅላይ የጦር አዛዥ ይቅርና መካከለኛ ማዕረግ እንዳለው መኮንን እንኳ ከወታደር ኋላ ወይንም በአማካኝ ሥፍራ መገኘት ሞት ይመስለው ነበር።
ለእናት አገሩ ኢትዮጵያ በሕይወቱ መስዕዋት ለከፈለላት ልጇ ለታላቁ አርበኛ ለሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ታሪኩ እንዳይጠፋና ተግባሩ በትውልዶች ሁሉ እንዳይረሳ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ለባለውለታው መኮንን በ1950 ዓ.ም. የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የጦር ትምህርት ቤት ታድሶ ሲመረቅ የመኮንኑ ጀግንነትና ባለ ውለታ ለመሆኑ ተመስክሮ ጥሩ የወታደር አዛዥ ከመሆኑም በላይ በአደረገው አመራር የሚያስደስት ጀብዱ ስለሠራ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን የጦር ሜዳይ ከሁለት ዘንባባ ጋር እንዲሁም ያንድ ዓመት ያርበኛነት ሜዳይ ከአንድ ዘንባባ ጋር ተሸልሟል። ከዚህ በተጨማሪ የጦር ትምህርት ቤቱ ውስጥ ሐውልት ቆሞለት በስሙም መጥሪያ የሚሆን የተማሪዎች መኝታ መንደር ተሰይሞለታል።
ይህንን ሁሉ ጀብዱ የፈጸሙት ኢትዮጵያዊ ጀግና በግፍ ሲገደሉ እድሜያቸው ሀያ አንድ አመት ከዘጠኝ ወር ነበር። ስማቸው ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ይባላል። ልብ በሉ! ሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ያንን ሁሉ ታሪክ የሰሩት የ21 አመት ልጅ ሆነው ነው። ከወረራው በኋላ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በገነት ጦር ትምህርት ቤት ውስጥ መታሰቢያ አቁመውላቸው ነበር። ለእናት አገራቸው መተኪያ የሌለው መስዕዋትነት የከፈሉት የነ በላይ ኃይለ አብ መታሰቢያ የሚገኝበት ታሪካዊው የሆለታ ገነት የጦር ትምህርት ቤት ኢትዮጵያን ለማፍረስና የትግራይን ሪፑብሊክ ለመመስረት በታገለው በወያኔው ሐየሎም አርአያ ስም ይጠራል።
ጀግናው ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ የተወለዱት በ1908 ዓ.ም. ሲሆን ትውልዳቸው ከመረብ ማዶ ከባህረ ነጋሽ ነው። እነ ኢሳያስ አፈወርቂ ኢትዮጵያ ቅኝ ገዛችን ብለው ሊወጓት ጫካ ቢገቡና ቢያደሟትም እነ ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ ግን ለእናት አገራቸው ኢትዮጵያ የሞት ጽዋን ተቀብለዋል።
ኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቷንና የጠላቶቿን ሁሉ የጡት አባት ጨካኙን ኢሳያስ አፈወርቂን በየ ሳምንቱ በክብር ስትቀበል ስለ እሷ የወደቀውን ጀግናውን ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብን ግን የምታስታውስበት አፍታ የላትም፤ አትፈልግምም! የሷ ጀግኖችና ክብር የሚገባቸው ሊጥሏት የተነሱት የሻዕብያው አምበል ኢሳያስ አፈወርቂና ደቂቆቹ ናቸው። ለዚህም ነበር ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ፤
ኢትዮጵያ አገሬ ሞኝነሽ ተላላ፣
የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ፤
ሲሉ ዘመን የማይሽረው ሀሳብ ቋጥረው ያለፉት!
ክብር ለታላቁ ጀግና ለኢትዮጵያዊው ሰማዕት ለሌተናት ኮሎኔል በላይ ኃይለ አብ!!









Saturday, May 22, 2021

ፓርቲ፤ መንግስትና ሀገርን መለየት ያስፈልጋል

 


የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የወጣት ማሀበር ፅ/ቤት  ግቢ በብልፅግና ማስታወቂያ ደምቆለል፡፡ እኔም ዛሬ እንኳን ብዝሃ -ፓርቲ ስርዓት ለመገንባት  በምንተፋተፍበት  ሰዓት ፤ በምርጫ ዋዜማ  የመንግስት ተቋማት ፤የከተማውን ወጣት የሚወክል መስሪያ ቤት በብልፅግና ማስታወቂያ ማሸብረቁ ግርምት ፈጥሮብኛል፡፡ ገዢ ፓርቲ መሆን ማለት ከጠቅላይነት  አባዜ መቼ ነው የምንላቀቀው ስል ለራሴ የማልመልሰው ጥያቄ  መለስሁ፡፡  ኢህአዴግ በገጠር  ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ፤ የእርዳታ እህል ሳይቀር የሚሰተው ለአባላቱና ለደጋፊዋቹ  ነው፤ ማይክሮ ፋይናንስ ጠቋማት በከተማ የሚደራጁት ደጋፊያቸውንና አባላቸውን ነው እያልን ክፉኛ ወቀስነው፡፡   ኢህአዴግ አውራ ፓርቲ ሆኖ አብጦ ያካሄዳቸው አምስት ምርጫዋች በሙሉ  (ከምርጫ 1997 ዓ/ም ውጭ) ምርጫ ሳሆኑ ኢህአዴግ  ለይስሙላ የሚያካሄዳቸው ፤ ዳኛውን የምርጫ ቦርድ  በቁጥጥር ስሩ አውሎ ወደ ምርጫ ውድድር የሚገባበት የይስሙላ ምርጫዋች እንደነበሩ የአደባባይ ሀቅ ነው፡፡

ዛሬ ኢህአዴግን  በህዝባዊ አመፅ ሸኝተን ከኢህአዴግ  ታድሰን ወደ ብልፅግና ፓርቲ  አድገናል፡፡ የአጋረችን የኢትዮጵያን ትንሳኤ  ለማብሰር በኢትዮጵያዊያን ህዝብ ድምፅ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ እንተክላለን ብሎ ቆርጦ የተነሳው ብልፅግና ፓርቲ ግን በአደባባይ እየሰራ ያለው  ከኢህአዴጋዊ አውራ ፓርቲ  እንቅስቃሴ ተለይቶ የሚታይ አይደለም፡፡   ኢህአዴጋዊ አውራ ፓርቲ  በመሪው ግለሰብ ተክለሰውነት ግንባታ ተጠምደው ፤ ተከታይ አመራር ማፍራት ተስኖቸው ፤ መሪው በሞተ ማግስት ተከታይ  (ተደማጭ አመራር ) ማፍራት ተስኖቸው በመጨረሻ የአቶ ሃይለማርያምን  “ስልጣን በቃኝ    ውሳኔ አስከትሎል፡፡  የብልፅግና ፓርቲ  ሊቀመንበር ዶ/ር አብይ አህድ  ከኢህዴግ ልምድ ባልተለየ  ፓርቲውና አብይ አህመድ እንዲቆራኙ ፤ አብይ አህመድ ከሌለ ብልፅግና የለም እስከሚመስል ድረስ እየተሰራበት ነው፡፡ የብልፅግናን የምርጫ ቅስቀሳ ቢልቦረርዶች መመልከት በራሱ  ለዚህ ድምዳሜ ማስረጃ ይሆናል፡፡ በኢዲስ አበባ እና በሌሎች ክልሎች የተተከከሉ ቢልቦርዶች  “በዶክተር አብይ ጥላ ስር የተሰበሰብን  ችግኝ እጩዎች ነን ምረጡን” የሚል  መልዕክት ይዘዋል፡፡

 አውራ ፓርቲ  እያበጠ እያበጠ  ሄዶ አምባገንን  እየሆነ የመሄድ እድሉ የሰፋ ነው ፡፡ በአገራችን በየጊዜው እየፈነዳ ያለው የሰላም መደፍረስ እና  የአካባቢያችን  ጂኦ-ፖለቲካ  ግጭት  በእንቅርት ላይ ጀሮ ደግፍ እንዲሉት  የምርጫ ፉክክሩ  ላይ   የራሱን ጥላ አጥልቶበታል፡፡  ምርጫ  ቦርድ ያወጣው የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ተስፋ ሰጭ ቢሆንም፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ግን መጭወን ምርጫ የሚያካሄድበት ድባብ በራሱ ነፃ ምርጫ ላይ ተፅኖ አለው፡፡ ዶክተር አብይ አብይ አህመድ  ስለ ህገ-መንግስታዊ  ለውጥ ሲጠየቁ ብልፅግና ህገ-መንግስታዊ  ማሸሻያ ለማድረግ በዴሞክራሴያዊ ምርጫ  ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ቃል -ኪዳን ማሰር አለበት  (መመረጥ) ያሉት  ቃል በብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎች እና የመንግስት መዋቅር በያዙት  እኩል የሚደገፍ ሃሳብ ከሆነ  የምርጫ ሂደቱ የመበለጠ አሳታፊ፤ ታማኝና ዴሞክራሲያዊ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

ተወዳዳሪ ፓርቲዎች በተጨባጭ  በሀገራችን ፓርቲ (ገዢ ፓርቲ) ፤ መንግስትና ሀገር የሚለው የተቀላቀለ ሃሳብ መሆኑን ተረድተው የምርጫ ቅስቀሳቸውንም ከዚህ አረዳድ መቅረጽ ይኖርባቸዋል፡፡  ገዢው ፓርቲ አባላቱንና ደጋፊዎቹን የሚያሰባስበው የመንግስትን መዋቅር በመጠቀም የሀገርን ሃብት ኢ-ፍታሃዊ በሆነ መንገድ በማከፋፈል ነው፡፡  የአዲስ አበባን የቤት ችግር ለመቅረፍ የተጀመረው ፕሮጄክት በአዲስ አበባ  ለገዢው ፓርቲ  አባላት በማከፋፈል መጠናቀቁን ጥናታዊ ሪፖርቶች አማክተዋል፡፡ በተቃራኒው  ተወዳዳሪ ፓረቲዎች አባላትና ደጋፊዎቻቸው ፓርቲያቸውን ለማደራጀትም ሆነ ለምርጫ ቅስቀሳ የሚሆን የሀብት ምንጭ የሚሆን ሃብት  ማዋጣት አለባቸው፡፡ ገዢው ፓርቲ  በፓርቲ አይዲዮሎጂ ያሰባሰባቸው አባላትና ደጋፊዎች እንዳሉት ሁሉ ፤ ተወዳዳሪ ፓረቲዎችም   ውስጥ የፖለቲካ ተሳትፎን ለጠባብ የግል ፍላጎት መጠቀሚያ ለማድረግ የሚሳተፉ አይጠፉም፡፡ኢህአዴግን  ገገማ የሆኑ አባላቶቹ አስወግዶ ታክቲካል ለውጥ አድርጎ ብልፅግና በሚል የዳቦ ስም እያጠቃ ያለ ገዢ  ፓርቲ  ነው፡፡  ብልፅግና ከኢህአዴግ በባሰ መንገድ እራሱን  የኢትዮጵያ አዳኝ አድርጎ እየሳላ ያለ ፓርቲ ስለሆነ  አባላቱና ደጋፊዎቹ   ይኸንን   እምነታቸውን ለማስፈፀም የበለጠ  ኢ-ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የመንግስትን መዋቅርና የሀገር ሃብት ለፓርቲያቸው እየጠቀሙ ይገኛሉ፡፡  ይኸነን ሁኔታ ለመለወጥ የብልፅግና ደጋፊዎችን  ማማለል እራሱን የቻለ የትግል ስልት ሆኖ መወሰድ አለበት፡፡

ተወዳዳሪ ፓርቲዎች የሀገር ውስጥ ደህንነት፤ የከተማ ልማት ፤ የትምህርት ልማት ፤የኢንዱስትሪ ልማት፤ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ  አማራጫቸውን ሲያቀርቡ በገዢው ፓርቲ ጥላ ስር ተጠልለው ፤ የፓርቲው መዋቅር ከገዢ ፓርቲነት ከተነጠለ የእነሱም ሕይወት ከአስትንፋሱ እንደሚነጠል ለሚያስቡ  በስም ብልፅግናዋች በተግባር ግን መዥገሮች ለሆኑ አባላትና ደጋፊዎች ማስተማመኛ መስጠት አለባቸው፡፡ ለእነዚህ መዥገሮች የሚሰጣቸው ማስተማመኛ (ይቅርታ) ተወዳዳሪ ፓርቲዎች አለን የሚሉት ደጋፊም ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን አለበት፡፡  ጥቅም ፍለጋ የመጣ  ደጋፊ ያሰባሰቡ ፤ በተራችን “መንግስት ከሆን” ፤ ስልጣን ከአገኘን  ብለው የተሰባሰቡ ካሉም ይበተናሉ፡፡

ለመዢገር ብልፅግናዎች የሚሰጣቸው ማስተማመኛ እንደሚከተለው ሊቀርብ ይችላል፡፡

Ø  የእኛ  ፓርቲ  የህዝብ ድምፅ ቢያገኝና መንግስት ቢመሰርት ፤ በፓርቲ አባልነት የተሰበሰበ የፓርቲ ጥማጥቅም  (ቤት፤ መኪና፤ ሌሎች) መንግስት ስንሆን  በምናቋቁመው አጣሪ ኮሜቴ ተለይቶ ቢያንስ ቤት የሌላቸው ብልፅግናዎች የመንግስት ቤትን እስካልበለፀጉ ድረስ አይነጠቁም፡፡

Ø  የፖሊስ፤ የደህንነትና የመከላከያ ተቋማትን ማፍረስ ማለት አገርን ማፍረስ ማለት ስለሆነ፤ እነዚህ  ተቋማት ላይ ምንም እንኳን ያለን እምነታችን የተሞላ ባይሆንም  ፤እነዚህን ተቋማት እኛ ተወዳዳሪዎች እነዚህ ተቋማት የበለጠ ፕሮፌሽናል ኢትዮጵያዊ ተቋማት እንዲሆኑ እንሰራለን እንጂ የብልፅግና ወታደር ብለን የኢህዴግን ስህተት አንደግምም በማለት ማረጋጋት ያፈልጋል፡፡

Ø  የእኛ ፓርቲ ቢያሸንፍ  የምንገነባው ዴሙክራሲያዊ ስርዓት ሀገር በቀል  ሆኖ ፤ ብዙሃን ራሳቸውን የሚሳስተዳድሩበት ፤ ህዳጣን መብት የሚከበርበት ይሆናል እጂ (Majority rule , minority right)  ፤ በሀረሪ ፤ በድሬዳዋ (50/50 እና 40/40/20  )፤ ቤኔሻንጉል፤ ሌሎች ክልሎችም የሚሰራበት የአፓርታይድ ስርዓት አይነት  ይወገዳል፡፡ ይኸን የሚሆነው ግን ኢትዮጵያዊያን ምሁራን በሰከነ መንገድ ፤ከየአቅጣጫው ተሰብስበበውና፤ መክረው ዘክረው በሚያወጡት ህገመንግስታዊ ሰነድ ይሆል፡፡

እነዚህን ማስተማመኛዋች  ወይንም እውነታዎች ተወዳዳሪዎች ቢያፈነዶቸው አንድም  እንቅፋቶችን ለመቀነስ ብሎም ደጋፊን ለማሰባሰብ ይረዳሉ፤ ሁለትም ሃቀኛ ደጋፊዎችን ለማወቀቅና  የማይደግፉአቸውንምንም ለማወቅ ይረዳል፡፡  ገዢው ፓርቲ መንግስትና ሀገር እየቀላቀለ በሚጠቀምበት ሁኔታ እና  ውስጣዊና ውጫዊ ግጭቶች ብዙሃኑ ላይ “መንግስት አለ ፤መንግስት የለም፤ ተጠቃን” የሚል ጥያቄዋች በሚመላለሱበት ወቅት ለተወዳዳሪዎች ምርጫ ማካሄድ እጅግ ፈታኝ ነው፡፡

Friday, March 1, 2019

የመቀሌ ምሽግ! አብራሃም ለቤዛ


የመቀሌ ምሽግ!
ትህነግ/ህወሓት መቀሌ መሽጎ የተለያየ እቅድ እያወጣ የፌዴራል መንግስትን እጅ ለመጠምዘዝ እየሞከረ ነው፡፡ ጊዜ መግዣ የመሰለው አመራጭ ሁላ በመደመርና ትዕግስት ፍልስፍና ለተለጎመው ለአብይ አህመድ አስተዳደር ፈተና ሆኖል፡፡   ዛሬ ትህነግ/ህወሓት በሚመራው ክልል በጉልበት በጠቀለላቸው የወልቃይት እና ራያ አማራ ህዝብ ላይ እልቂተ እያደረሰ ይገኛል፡፡  መቀሌ የመሸገው ሃይል የመጨረሻ ካርዱን የትግራይ ህዝብን ጭዳ ለማድረግ የጦርነት ዝግጅት እደረገ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የመጣውን አቃፊ የለውጥ ጅማሮ ከጅምሩ እያጣጣለ ፤ትህነግ/ህወሓት  የማይዘውራት ኢትዮጵያ በአፍንጫ ትውጣ እያለ ነው፡፡ እኛ የገነባባት ኢትዮጵያ ካላከበረችን ፤ የትግራይ ሪፐፕሊክ መስርተን ከጎረቤት ኢትዮጵያ በተሸለ ከጎረቤት ሱዳን  ጋር  እንወዳጃለን እያሉ ነው፡፡  በ27 ዓመት ዘርፈው ያጎጎዙት ሃብት የትግራይ ሪፐፕሊክ ለመመስረት እና በእራሳችን ለመቋም ያስችለናል እያሉ ነው፡፡  ትህነግ/ህወሓት እራሱን የትግራይ ህዝብ ጠበቃ አድርጎ ሲያቀርብ ፤ በትህነግ/ህወሓት ቀንበር ስል ያለው የትግራይ ህዝብ ስሜቱን የሚገልፅበት ምንም ምርጫ የለውም፡፡ አምባገነኖች የእራሳቸውን ድርሰት በማንበብ ስለሚፅናኑ‹‹ ትህነግ/ህወሓት ከተነካ የትግራይ ህዝብ ቀፎው እንደተነካ ንብ ሆ ብሎ ይነሳል›› በሚል ቅዠት ውስጥ ገብተዋል፡፡
እቴጌ ጣይቱ   የጦርነትን  አስከፊነት  እና የነፃነትን አስፈላጊነት ከመቶ አመት በፊት  በዚህ ሀረግ ነበር የገለፁት፡፡‹‹ እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም፡፡ ሆኖም ይህን ኢትዮጵያን የኢጣሊያ ጥገኛ (ውጫሌ ውል) የሚያደርግ ውል ከመቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ››   ምንም እንኳን ጦርነት አስከፊ እና አጥፊ ቢሆንም አያቶቻችን የነፃነት ትርጉም ስለገባቸው ፤ በመካከላቸው ያለ ልዩነት ትተው፤ እንዲሁም ከንጉስ ሚኒሊክ ጋር ቅራኔ የነበራቸው የጦር አበጋዞች ሳይቀር ወራሪውን ሃይ ለመመከት ተሰልፈዎል፡፡ አፄ ሚኒልክም ‹‹ አመልህን በጉያህ ፤ ስንቅህን በአህያህ  ይዘህ ተከተለኝ ›› የሚል ጥሪ ነው አቃፊ የሆነና ይቅርታ ታከለበት አርቆ አሳቢነታቸው ያሳየ አዋጅ ያስተላለፉት፡፡
በውጫሌ ውል ሸፍጥ ምክያት የተቀሰቀሰው ጦርነት በመጀመሪያው አውደ ውጊያ  አምባላጌ ተራራ ላይ የተጠላትን ጦር ካስለቀቀ በኋላ ሁለተኛው ግንባር የመቀሌን ምሽግ ማስለቀቅ ነበር፡፡ የጠላት ጦር የእንዳ እየሱስን ተራራ ደጀን አድርጎ በመቀሌ ላይ የሰራው ምሽግ በግንብ ፤ ሽቦ አጥር የተጠናከረ ሲሆን ፤ በባዶ እግሩ የዘመተውን የሃበሻን ጦር ለመመከት የጠላት ጦር በፋሽኮ ጠርሙስ ስብርባሪ ምሽጉን አጠናከሮል፡፡  የመቀሌ  ምሽግን ለመስበር በወገን ጦር ላይ ከፍተኛ የሆነ የህይወት መስዋትነት አስከፍሎል ፡፡ በዚህ መሃል በከአውደ ውጊያው ያሉት እቴጌ ጣይቱ  ከጠላት ጦር የተገኘ የስለላ መረጃ ይደርሳቸዋል፡፡ ይኸውም የጠላት ጦር ከወገን ጦር አልፎ ከሚሄድ ምንጭ ውሃ እንደሚጠጣ፡፡
እቴጌ ጣይቱ ለጠላት ጦር የሚሄደው የምንጭ ውሃ የማገድ  እቅዳቸውን ምንጩ በማስጠለፍ እና ምንጩን በተጠናከረ የወገን ጦር በማስጠበው የጠላትን ጦር ከውሃ እቅረቦት ውጭ አደረጉት፡፡ የጠላት ጦር ለራሱም ሆነ ለጋማ ከብቶቹ ውሃ ማግኘት ስለልቻለ ፤ ተደላልድሎ የያዘውን ምሽግ ሊለቅ ችሎል፡፡ ሴት አያቶቻችን ከመቶ አመት በፊት እንደዚህ ብለጠት በተሞላበት ሁኔታ አመራር እየሰጡ የአገርን ነጻነት ጠብቀዎል፡፡ እቴጌ ጣይቱ የወገን ጦርን ስንቅ በበላይነት እያስባበሩ ከአንድ ሺ ኪሎ ሜትር ባለይ በእግር ተጉዟ ለውጊያ የሚሰለፍ ሰራዊት ማፍራት ችለዎል፡፡
ዛሬም በኢትዮጵያ በመቀሌ የመሸገው  ትህነግ/ህወሓት በኢትዮጵያ ለይ ያቀደውን የጦርነት እቅድ የሚያከሽፍ እንደ ጣይቱ ያሉ ብልህ የዘመናችን ሴቶችን እንሻለን፡፡  ሴቶች የጦርነትን አሰከፊነት ያውቁታል ፤ የነፃነትን ጥቅምም እንደዚሁ፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ጣይቱን ፈለግ በመያዝ በኢትዮጵያ የመጣውን የነፃነትት የእኩልነት የተስፋ ጉዞ በሙሉ ልብ ሊደግፉት ይገባል፡፡ ይኸ ማለት ያለፈውን የጭቋና ስርዓት ፤ አግላይ ስርዓት ለመመለስ በመቀሌ የመሸገው ስርዓት ማውገዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የትገራይ እናቶች የጦርነትን አስከፊነት በደንብ ያውቁታል፡፡ ትህነግ/ህወሓት ትግራይ ተደፍራለች ፤ ተከባለች ለሚለው ጥሪ  ትህነግ/ህወሓት ሰከን ብሎ በእኩልነት ላይ ለምትመሰረት ኢትዮጵያ ተገዢ እንዲሆን ሊያሳስቡት ይገባል፡፡
‹‹የጎበዝ እናት ታስታውቃለች
፤አፋፍ ላይ ሆና በለው ትላለች››
የዘመናችን ሴቶች /እናቶች ከጦር ሜዳ ውለው የሞራል  ሆነ የአካል ስንቅ   መስጠት ላይጠበቅባቸው ይችላል፡፡  የሞራልም ሰንቅ ማዘጋጀትም ሆነ የአካል ስንቅ ማዘጋጀት  ፤ ምናልባትም ዘመናዊ  መንገድ  መስራት አስፈላጊ ስለሆነ፡፡ ነገር ግን የኢትዮጵያ ሴቶች/እናቶች  አበክረው ስለ ሰላም  መስበክ ይኖርባቸዋል ፡፡ በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ሰላም፡፡ አንዱ አንዱ ደፍጥጦ፤ ጭጭ አድርጎ የሚመጣ ሰላም  (Like the peace maker bomb) ሳይሆን በመከባበር የሚመጣ ሰላም፡፡ አርቲስ ማሪቱ ለገሰ  ስለ ሰላም ጥሩ አድርጋ ተጫውታለች፡፡ 
ሰላም ሰላም ቢሉት  ሰላም ለአፍ ይሞቃል፤ 
በትግል ያልተገኘ ከጦርም ይልቃል ፤
የሽንፈት ሰላም ግን ከሽብር ይከፋል፤
የሽንፈት ሰላም ግን ከሽብር ይከፋል፡፡
የኢትዮጵያ ሴቶች/እናቶች  የትግራይ  ሴቶች/እናቶች  ስለ ሰላም መስበክ አለባቸው፡፡ የተገኘውን መድረክ መጠቀም አለባቸው፡፡  የሰላም ሚኒስቴር  አቋቁመናል፤ አስር ሴት የካቤኔ ሚኒስቴር ሰይመናል፤ ወዘተ፡፡ ሴቶች ስለ ሰላም በተግባር አሁኑኑ ያስፈልጋል፡፡




Tuesday, February 12, 2019

የመስኩ ላይ ቁርሾ! !!!ጃኖ Mengistu Zegeye



ሲጀምሩ ፤
ሁለቱም ቆርኬዎች ፤
አብረው ከኖሩበት ፤
ከሚያምረው መስክ ዳር ፤
እየጋጡ ነበር ፤
ከጨፌው ማሳ ላይ ፤ እየፈነደቁ ፤
ድንገት ሳይታሰብ ፤
እነ ተኩላዎች ፤
ወዳጅ ዘመድ መስለው ፤ ወደዚያ ዘለቁ ።
ቆርኬዎቹ ዘንተው ፤
ሳር ከሚግጡበት ፤
ደረሱ ተኩላዎች ፤ እየተፋነኑ ፤
ውሃ በሞላው አፍ ፤
የጨፌውን ማማር ፤
የጋጮቹን ገላ ፤ እያስተነተኑ ፤
የተኩላ መንጎች ፤
እንኳን በስጋቸው ፤
በተቆላለፈው ፣ በቀንዳቸው ቀኑ ።
ቆርኬዎቹ ጠግበው ፤ እስኪፈነጥዙ ፤
እነ ተኩላዎች ፤
ሳሩ ላይ ዋሉበት እየተሟዘዙ ።
ጀመሩ ቆርኬዎች ፤
በጥጋብ ጀመሩ ቀጠሉ ማስካካት ፤
ተኩላ ተናቃ ፤
በጨዋታ መሃል ሸር ለማስገባት ።
እንደዚህ አላቸው ተኩላ አባ ሴራ ፤
ከአያት ቅም አያቶች ታሪክ ስናጣራ ፤
አለቃ ሚሆነው የቆርኬዎች አውራ ፤
ታግሎ የጣለ ነው ፤
ተፋልሞ ሚገዛ ከገጠሙት ጋራ ።
ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ጠቅልሎ ፤
በቀንዱ ጀመረው ፤
ካንደኛው ትከሻ አንዱ ቆርኬ ዘሎ ።
ተኩላ ዳር ቆማ ፤
በጭብጨባ በአጀብ ፤
በል በለው ትላለች ፤ በክፋት አንደበት ፤
ጀግና ማለት በኛ ፤
የጫካው አርበኛ ፤ የሚዘመርለት ፋኖ እየተባለ ፤
ቀንድን በቀንድ ይዞ ፤
አንገቱን ጠምዝዞ መሬት ላይ የጣለ።
በግብግብ መሃል ፤
ገራገር ቆርኬዎች ፤
የተኩላን ፊሽካ ፤ ሰምተው ተናነቁ ፤
ቀንዳቸው ተጣልፎ ፤
ሁለቱም ሜዳው ላይ ዘፍ ብለው ወደቁ ።
በተጠለፈ ቀንድ ፤ በተገመደ አንገት ፤ ወድቀው ተጋጠሙ ፤
ራስ በራሳቸው በጀመሩት ትግል ማንም ሳያሸንፍ ሁለቱም ደከሙ ፤
በተኩላ ተንኮል አብሮ አደግ ቆርኬዎች ሞትን ተሸለሙ ።
ይህን ያየ ቆርኬ ፤
የወንድሞቹ ሞት ፤ በተኩላዎች ሴራ መሆኑን ተረድቶ ፤
ከሞቱበት ሳር ላይ ፤
ካለው ትልቅ ዛፍ ላይ ፤
እንዲህ ብሎ ጻፈ ብእሩን አውጥቶ ።
ሰፊ መስክ ሳለ ፤
ሰፊ ጨፌ ሳለ ፤ በዚህ በመንደሩ ፤
ያንዲት እናት ልጆች ፤
አንተ ወግድልኝ
እኔ ነኝ አለቃ ፤
እኔ ነኝ ባለ ሹም በሚሉት አምቡላ ስለተሳከሩ ፤
ሞሰቡ ሳይቸግር ፤
እኔ በሚል እሳት ፤ ተበላልተው ቀሩ ።

የመስኩ ላይ ቁርሾ! !!! ጃኖ Mengistu Zegeye

የመስኩ ላይ ቁርሾ! !!! ጃኖ Mengistu Zegeye
ሲጀምሩ ፤
ሁለቱም ቆርኬዎች ፤
አብረው ከኖሩበት ፤
ከሚያምረው መስክ ዳር ፤
እየጋጡ ነበር ፤
ከጨፌው ማሳ ላይ ፤ እየፈነደቁ ፤
ድንገት ሳይታሰብ ፤
እነ ተኩላዎች ፤
ወዳጅ ዘመድ መስለው ፤ ወደዚያ ዘለቁ ።
ቆርኬዎቹ ዘንተው ፤
ሳር ከሚግጡበት ፤
ደረሱ ተኩላዎች ፤ እየተፋነኑ ፤
ውሃ በሞላው አፍ ፤
የጨፌውን ማማር ፤
የጋጮቹን ገላ ፤ እያስተነተኑ ፤
የተኩላ መንጎች ፤
እንኳን በስጋቸው ፤
በተቆላለፈው ፣ በቀንዳቸው ቀኑ ።
ቆርኬዎቹ ጠግበው ፤ እስኪፈነጥዙ ፤
እነ ተኩላዎች ፤
ሳሩ ላይ ዋሉበት እየተሟዘዙ ።
ጀመሩ ቆርኬዎች ፤
በጥጋብ ጀመሩ ቀጠሉ ማስካካት ፤
ተኩላ ተናቃ ፤
በጨዋታ መሃል ሸር ለማስገባት ።
እንደዚህ አላቸው ተኩላ አባ ሴራ ፤
ከአያት ቅም አያቶች ታሪክ ስናጣራ ፤
አለቃ ሚሆነው የቆርኬዎች አውራ ፤
ታግሎ የጣለ ነው ፤
ተፋልሞ ሚገዛ ከገጠሙት ጋራ ።
ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ጠቅልሎ ፤
በቀንዱ ጀመረው ፤
ካንደኛው ትከሻ አንዱ ቆርኬ ዘሎ ።
ተኩላ ዳር ቆማ ፤
በጭብጨባ በአጀብ ፤
በል በለው ትላለች ፤ በክፋት አንደበት ፤
ጀግና ማለት በኛ ፤
የጫካው አርበኛ ፤ የሚዘመርለት ፋኖ እየተባለ ፤
ቀንድን በቀንድ ይዞ ፤
አንገቱን ጠምዝዞ መሬት ላይ የጣለ።
በግብግብ መሃል ፤
ገራገር ቆርኬዎች ፤
የተኩላን ፊሽካ ፤ ሰምተው ተናነቁ ፤
ቀንዳቸው ተጣልፎ ፤
ሁለቱም ሜዳው ላይ ዘፍ ብለው ወደቁ ።
በተጠለፈ ቀንድ ፤ በተገመደ አንገት ፤ ወድቀው ተጋጠሙ ፤
ራስ በራሳቸው በጀመሩት ትግል ማንም ሳያሸንፍ ሁለቱም ደከሙ ፤
በተኩላ ተንኮል አብሮ አደግ ቆርኬዎች ሞትን ተሸለሙ ።
ይህን ያየ ቆርኬ ፤
የወንድሞቹ ሞት ፤ በተኩላዎች ሴራ መሆኑን ተረድቶ ፤
ከሞቱበት ሳር ላይ ፤
ካለው ትልቅ ዛፍ ላይ ፤
እንዲህ ብሎ ጻፈ ብእሩን አውጥቶ ።
ሰፊ መስክ ሳለ ፤
ሰፊ ጨፌ ሳለ ፤ በዚህ በመንደሩ ፤
ያንዲት እናት ልጆች ፤
አንተ ወግድልኝ
እኔ ነኝ አለቃ ፤
እኔ ነኝ ባለ ሹም በሚሉት አምቡላ ስለተሳከሩ ፤
ሞሰቡ ሳይቸግር ፤
እኔ በሚል እሳት ፤ ተበላልተው ቀሩ ።

Friday, September 14, 2018

History 101: Fiction and Facts on Oromos of Ethiopia

(a guide for foreign journalists on Oromos and Ethiopian history)
Oromo, Ethiopia
Courtesy: ayyaantuu.com

(ADAMA, Ethiopia) - Recently, the Qatar-based media al Jazeera has published several articles concerning the Oromo people of Ethiopia. (http://www.aljazeera.com/indepth/opinion/2013/07/2013714133949329934.html) It is the first international media outlet to extensively report on our people and it should be praised for bringing our cause to the world stage.
One of the benefits of this exposure is it forces Ethiopian authorities to address human rights abuses in the country and to let them know that the world is watching. Oromos and other Ethiopians have been struggling for equal rights and democracy for decades. While it is important to report about Oromo people' background and historical perspectives, it is however vital that we report accurate information. Instead of benefiting us, reporting inaccurate or biased information can actually harm our struggle for democracy. Instead of creating national consensus and peace, it can instigate bitterness and anger.
One of the reasons al Jazeera reported inaccurate information about Oromo history is because it depended on one-sided sources, especially from members or supporters of Oromo groups outside of Ethiopia (diaspora OLF, OFDM etc). But nobody can blame al Jazeera media because most people inside Ethiopia would be too scared to speak or contribute. The only option al Jazeera or any foreign media has is to use diaspora/refugee/external sources outside Ethiopia. This is a dilemma all foreign media outlets face while reporting about third-world countries like Ethiopia.
For educational purposes, some corrections are provided below to fix inaccuracies reported on al Jazeera media regarding Oromo history and our struggle for democracy. The corrections below are supported by non-political scholars, but they might be rejected by biased politicians (both from ruling party and from opposition party) for the obvious reasons. However, they are based on historical textbooks, European authors and scholarly accounts.


Fiction #1:

"Between 1868 and 1900, half of all Oromo were killed, around 5 million people"

Fact #1: 
This is one of the most repeated inaccuracies, usually told by Secessionist Oromos, radical ethno-nationalist politicians outside the country or pro-OLF history revisionist websites like gadaa.com et al. However, the undisputed fact is that even the total Ethiopian population (the sum of dozens of ethnic groups) was much less than 5 million in the late 1800s, let alone one ethnic group being 10 million. So claiming that 5 million ethnic Oromos were killed by Emperor Menelik's forces does not add up. The truth is several thousand Oromos were in fact killed during battles of that era. It was not a "genocide" as some politicians claim but it was a massacre of the ill equipped southern forces defeated by the Shewan military of Emperor Menelik which had more European weapons. Throughout those decades, the truth is more Oromos were killed by other Oromos than by non-Oromos because competing Oromo Clans often traded for weapons to have an upper hand against their local competitors, who were often their fellow Oromo and Sidama neighbors.  And it was not the first lop sided victory of that era in Africa because various communities from all corners of Ethiopia had attacked one another during the "resource battles" and whichever group had more modern weapons had the upper hand. To summarize, Professor Mengistu Paulos of Jimma University said it best when describing right-wing Oromo liberation philosophy:-- 

"Most fictional accounts of 'Oromo history' blindly accepted as facts by some misled people are manufactured by former politicians turned Pseudo-historians  like OLF writer Asafa  Jalata, who is renowned for abuse of paraphrasing, often with out-of-context citations. For example, while quoting the 19th century Russian Alexander Bulatovich (who provided an 'educated guess' of annihilation of almost half Ethiopian population by disease, famine and war, including internal conflict between Oromo clans and with Abyssinians), the OLF-writer Asafa Jalata infamously claimed half Oromo population was killed by 'evil' Amharas.  This was purposely done by Mr. Jalata to create a foundation for ethnic hatred between Oromos and Amharas. Ironically, even Mr. Bulatovich himself never had the capacity nor the legitimacy to do a reliable census, as he spent just a couple of months walking around Oromia and hunting elephants in 1890s."


Fiction #2:

"…. largely Muslim Oromo people"


Fact #2:

This is a phrase seen in some media outlets but not most. Oromo people have never been a predominantly muslim people. In fact, both Christianity and Islam is not our ancestral religion because we have practiced an indigenous traditional religion for centuries before. Gradually, Islam and Christianity were both adopted (during Oromo migrations) by us and imposed (during conquest of our lands by Abyssinian/Christians & Somalis/Islam)  on us thru out history. Even today, both the two major religions have equal representation among Oromos. The latest official 2007 census showed that around 48% of Oromos practice Christianity (Both Orthodox & Protestant) while around 47% of Oromos practice Islam. Yet, word on the ground is that the Islam population might soon surpass Christianity among Oromos in the future because Orthodox Christianity is decreasing inside Oromia. 

Fiction #3

"Abyssinians labelled Oromos the derogatory word 'Galla'"

Fact #3:

For many decades, this false statement has been used by Oromo separatists to create emotional resentment among Oromos against Semitic Abyssinians (Amharas, Tigrayans and Gurages).  The fact is the derogatory word "Galla" was first used by Arab and muslim Somalis to describe Oromos as "gal" meaning "outsiders" and "Pagans." Muslims used this label during Oromo migration because Oromo people had their own religion which the Muslims believed was paganism. Nonetheless, this derogatory word was gradually adopted and used by other Ethiopians. 

Fiction #4:

"Oromos were colonized by Emperor Menelik"

Fact: #4

Another popular claim made by secessionist Oromo politicians (and usually repeated by foreign journalists) is the fiction that Oromo people (as a whole ethnic group) were colonized by another ethnic group. Usually, the slogan goes "Abyssinians colonized Oromos" etc. This claim is popular among the Oromo Liberation Front (OLF) organization and consequently among some Diaspora Oromo nationalists living in America and Europe.  While a different version or a re-arrangement of the wording might still be true…in general, the Oromo nation as a whole was never colonized by another Ethiopian ethnic group. To start with, even a united one Oromo nation did not exist at those times. All non-political historical textbooks show the existence of battles between multi-ethnic BUT monolingual communities for many centuries through out Ethiopia. Even in northern Ethiopia (traditional "Abyssinia") Oromos have migrated and mixed so much with Tigrayans, Amharas, Afars etc for centuries that the "Abyssinia" state itself was never a one-ethnic state. In fact, even around the 1700s, Rayya Oromos and Yejju Wallo Oromos conquered and dominated a portion of Amharas and Tigrayans; and thus made Afan Oromo the official language of Abyssinia for that brief period. Meaning: clans and ethnic groups have mixed up in Ethiopia for over a millennium but the dominant ethnic group always imposed its language since it was convenient. This linguistic domination however was not always as exploitive and as vilified as it is today; because many of the ethnic groups living along trade centers and trade routes often spoke the languages of other ethnic groups already, because there was financial or commercial incentive to do so. This is the background of the region. Therefore, when it comes to the Emperor Menelik era, all historians have argued that it is more factual to say a predominantly Amharic language speaking community gradually conquered a predominantly Afan Oromo language speaking community in the 1800s. So this does not mean an Oromo ethnic group was conquered by an Amhara ethnic group. In fact, just like Amharas of the north were divided,Oromos were also divided and in conflict among themselves. The obvious evidence for this comes from the fact that the Amhara Emperor Menelik was imprisoned by other Amhara regional kings when he was younger. And when he was freed, Oromo clans were also in fierce battles amongst each other, so much so that the Tullama Oromo, Limmu and Macha Oromos created an alliance with the Shewan Amharas of Menelik, leading to the infamous battles of 1880s that led to this said alliance easily crushing the non-allied Oromos in various bloody wars. In short, Oromos as a one whole were never colonized by exclusively non-Oromos. In fact, the original founders of the OLF organization themselves never believed it so they did not emphasize the word "colonization" in the beginning. But in the mid-1970s, OLF leaders needed to mobilize Oromos against Emperor Haile Selassie (who was half Oromo himself) and to justify the call for "Oromia independence" from "colonial Ethiopia." Therefore OLF had to create a bad cop-good cop scenario for their convenience and simplified history for their people to create national resentment. This helped OLF to portray Oromos as suddenly being colonized by this foreign ethnic group (Amhara) that we (Oromos) have never came in contact with before.  This is common tactic used by national liberation movements around the world. The truth that most Ethiopians know is that Shewa based Oromos and Amharas (ethnically mixed Ethiopians) were the main creators of modern Ethiopia. In his book "Who are the Shoans," the historian and anthropologist, Dr. Gerry Salole once summarized that: "In terms of descent, the group that became politically dominant in Shewa (and subsequently in Ethiopia) was a mixture of Amhara and Oromo."   


In Conclusion, the above are 4 of the main issues that create confusion for foreign journalists who report on Oromo people and Oromo politics in Ethiopia.  While it is vital that al Jazeera and other media outlets cover the current suffering of Oromos and other Ethiopians, it is necessary to report responsibly. Otherwise, creating confusion and resentment between the younger Ethiopian population causes more problems than solutions. In reality, not just Oromos, but all Ethiopians have suffered under several governments and the only way they can achieve freedom and lasting democracy is when united, not when divided by tribes or not when being polarized by historical lies presented as truth.  It is important that foreign media outlets make corrections or report accurate information to avoid inflammatory statements that are destructive and counter productive against Oromos and all Ethiopian people' ongoing struggle for democracy, development and justice.


Feqadu Lamessa is a former Adama University professor and writer