Followers

Wednesday, December 24, 2014

ስደትን የሙጥኝ ማለት ወይስ በክብር ከቀዬ መኖር?




የተስፋዎ ምድር እስራኤል ዛሬ የተስፋ ምድር ሳትሆን ከ60ዓመት በፊት ዜጎቾ እንደጨዉ ዘር ተበትነዉ የሂትለርን ጭፍጨፋ ጭምር ለማስተናገድ ተገደዎል፡፡ ዛሬ እስራኤል መሰል ታሪኳን አስቀድማ ለመከላከል ለሚሰነዘርባት ጥቃት የምትወስደዉ እርምጃ ከእጥፍ በላይ ነዉ፡፡ የኒዉክለር መሳሪያ ባለቤት የሆነችዉስ ለማስፈራራት ሳይሆን ይቀራል፡፡ በጉልበት ለሚያምን ዓለም ጉልበት፡፡
ዛሬ እስራኤል ያሳለፈችውን የመከራ ዘመን ተራዉ ተከባብሮ መኖር ላልቻለ አገር ዜጋ ነዉ፡፡ በአገሩ መኖር  ባለመቻሉ የተስፋዎን ምድር እስራኤልን ለመግባት የግብፅን የሲናይ በርሃ አቆርጠዉ የሚሄዱ የኤርትራ፣ ሱዳንና ኢትዮጵያ ስደተኞች በግብፅ ድንበር ጠባቂዎች እጅ ላይ ሲወድቁ ሰብዓዊነት የጎደለዉ አስከፊ ስቃይ ይጠብቃቸዎል፡፡ በጣም ዘግናኙ  ደግሞ የበደዊን ጎሳዎች እጅ ላይ ከወደቁ  ነዉ፡፡ የሰውነት ክፍሎቻቸዉ በማፊያ ስራ ላይ በተሰማሩ ተንቀሳቃሽ ዶክተሮች (ድምበር የለሽ ዶክተሮች አላልሁም) ኩላሊትና ጣፊያ እየወጣ ይሸጣል፡፡ ጎበዝ ይህን ዘግናኝ አጭር ፊልም ስታዩ (ማስፈንጠሪያዉን በመጫን) ምን እንደሚሰማችሁ መገመት አያዳግትም፡፡ እኔን የተሰማኝ ሃዘንና ቁጭት ነው፡፡ ኢትዮጵያን የሁላችንም፣ዜጎች የሚኖሩባት፣  ስደትን የማይመርጡባት ምቹ አገር ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡ ለዚህ ያበቃንን ዘረኛዉን የወያኔ መንግስት በመታገል፡፡ አበቃሁ፡፡





https://www.youtube.com/watch?v=LRXy4TfRY5k


                                                                

Monday, December 8, 2014

ሁለቱ የደርጉ መቶ አለቆች!!!

የዛሬዉ ታሪካችን በቅጡ ካልተመዘገበ ነገ በተረት ተረት መልክ እንደሚወራ እርግጠኞች መሆን እንችላለን፡፡ ታሪኩ ሙሉ ካልሆነ ፤ አንባቢን ማደናገር በማለት ከማለፍ ይልቅ ማወቅ የተቻለዉን ያህል በማለት ለሌሎች ባለተራዎች በመተዉ እነሱዉ እራሳቸዉ እንዲቆፍሩት ማድረግ የተሸለ ነዉ፡፡  የታሪኩን ጭብጥ ለመረዳት ነበር ቀጥር አንድ የገስጥ  ተጫነን መፅሃፍ ማንብብ መልካም ነዉ፡፡
ደርግ ሰኔ 21 ቀን 1966 ዓ/ም ከተራ ወታደር አስከ ሻለቃ  በሚደርሱ መለዮ ለባሾች  በ4ኛ ክፍለ ጦር ግቢ ሲመሰረት የአቢዮቱ አንዱ ገጽታዉ በማዕረጋቸዉ ከፍ ከፍ ያሉትን ያገለለበት ምክንያት ባለትልቅ ማዕረጎች ከንጉሳዊ ስርዓት የሚያገኙት ጥቅማጥቅም  የተሻለ በመሆኑ የአቢዮቱን ሂደት በሙለ ልባቸዉ አይተባበሩም ወይም ያሰናክላሉ በማለት  ነዉ፡፡
110 ገደማ የሚደርሱ አባላት ያሉት ደርግ ''ያለምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም!!!''  የሚል መፈክር አንግቦ  ወሳኝ የሆኑ አገራዊ ዉሳኔ አሳልፎል፡፡ የመሬት ለአራሹን ጥያቄ በመርህ ደረጃ የመለሰበት በዋናነት የመጠቀስ የደርጉ እርምጃ ነዉ፡፡ ''ያለምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም !!!'' መርህ ግን ብዙም ሊዘልቅ አልቻለም ፡፡ ደርግ 53 የሚደርሱ የንጉሱ ባለስልጣናትንና የእራሱን ሰዎች በጅምላ ገደለ፡፡
ደርግ የዝቅተኛ መኮንኖች ጥርቅም እንደመሆኑ እርስ በርስ ለመደማመጥ አልቻለም፡፡ ይልቁን ይህ የ110 ሰዎች ስብስብ የደርግን ጡንቻ ለመቆጣጠር የመጣበትን የጦር ክፍል ተንተርሶ አልያም ተቀናቃኙን ጠልፎ የሚጥልበትን ሴራ በመጎንጎን ሁሉም የእየራሱን ቡድን የበላይነት ለመቆጣጠር ሙከራ በሚያደርግበት ሰዓት ነዉ ከፊሉ ደርግ ከሁለቱ መቶ አለቆች ቡድን ጋር የተላተመዉ፡፡ ሁለቱ መቶ አለቆች በዉቀቱ ካሳ (የክቡር ዘበኛ ተወካይ) እና ስለሺ በየነ  (የአየር ወለድ ተወካይ) የሃረር ጦር አካዳሚ ምሩቆች በመሆናቸዉ የደርግ መዘዉር ከሻለቃ መንግስቱ የሆለታ ገነት ጦር ትምህርት ቤት ምሩቅ እንዲወጣና ወደ እነሱ ቡድን እንዲሄድ ይፈልጋሉ፡፡
ሁለቱ መቶ አለቆች የሻለቃ መንግስቱ ቡድን ተቀናቃኞቹን በፀረ-አቢዮት ሰበብ አንድ ሁለት እያለ ሲለቅማቸዉ ታዲያ ወደ ትዉልድ አካባቢያቸዉ ጎጃም ፤ማቻክል ወረዳ፤ ትሳስዳር ቀበሌ ለአንደኛዉ መቶ አለቃ የስጋ ዝምድና ካለዉ ፊዉዳል ዘንድ ሄደዉ መሸጉ፡፡  መቶ አለቆቹ የመሸጉት ምናልባት ለአጭር ጊዜም ቢሆን ህይወት ለማቆየት ብለዉ እንጂ  ከዳር ዳር በተዛመተዉ አቢዮት ፀረ-ደርግ አቋም ይዘዉ ከለላ እናገኛለን በሚል ቅዠት አይመስለኝም፡፡
በደርግ ስብስብ ቀስ በቀስ እየጎሉ የመጡት ሻለቃ መንግስቱ (ጠላቶቻቸዉን አድብተዉ እስቲያጠቁ ድረስ ጥርሳቸዉን ብልጭ እያደረጉ የማዘናጋት ልዩ ተሰጥኦ እንዳላቸዉ የነበር መፅሃፍ ደራሲ ይገልጾቸዎል፡፡) እነዚህ ሁለቱ መቶ አለቆች ሲሰወሩ የሚደመስሳቸዉ ሃይል ልኮ ነበር፡፡
ይህን  አባቴ የተረከልኝን ታሪክ ነዉ ላዎጋችሁ የመረጥሁት፤ ደርግ የላከዉ ሃይል ጎጃም  ያረፈዉ በማቻክል ወረዳ ፤ አማኑኤል ከተማ ፤ አማኑኤል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነበር፡፡   አፄ ቴዎድሮስ የኢትዮጵያን ወታደር ለማዘመን ድርጎ እንዲኖረዉ ብዙ ጥረት ካደረጉ በኋላ  በንጉስ አፄ ሃይለ ስላሴ  ጊዜ ጀምሮ ዘመናዊ የኢትዮጵያ ወታደር የተገነባ ቢሆንም በደርግ ሁለቱን መቶ አለቆችች እንዲደመስስ የተሰማራዉ ጦር ግን  በትሳስዳርና አካባቢዉ ቀበሌ አርሶ አደር ሃብት ላይ ዘመተ፤ ከብቶቹን እየነዳ አማኑኤል ከተማ በሚገኘዉ ካምፑ ፈንጠዝያ አደረገ፡፡

ይህ ሃይል ከሳምንታት ቆይታ በኋላ ነዉ ሁለቱን መቶ አለቆች በግዳይነት የጣለዉ፡፡  አስጠልለዎቸው የነበሩትን ፊዉዳል ግን ''የአቢዮቱ ተጠቃሚ'' ለነበረዉ የአርሶአደር የቤት ስራ  ሰጥተዉ ተመለሱ፡፡ ፊዉዳሉ ብዙ አልቆዩም በአርሶአደር እጅ ከሸጥ ውስጥ ከተደበቁበት ተገደሉ፡፡  እነዚህ መቶ አለቆች ከክብር ዘበኛ እና አየር ወለድ የጦር ክፍሎች ተወክለዉ ሲሄዱ የኢትዮጵያ አቢዮት የለዉጥ አካል ሊሆኑ ነበር፤ አቢዮት ልጆቾን ትበላለች እንደሚባለዉ ከአያሌ የአቢዮቱ ሰለባዎች ሁለቱ  ሆኑ፡፡ እነዚህ መቶ አለቆች በተገደሉበት አካባቢ የተቀበሩ ሲሆን ዛሬ ድረስ ገብስማ  ቀበሌ ዉስጥ የደርጎች መቃብር የሚባል ቦታ አለ፡፡

Thursday, October 2, 2014

አስጠራዡ ሲጠረዝ!!!

የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢኮኖሚ ድፕሎማሲ አተኩሮ እንደሚሰራ እና ባላ ሃብቶችን ከየሃገራቱ  እንደሚስብ መደስኮር ከጀመረ ሰነባብቶል፡፡ ነገር ግን ይህ እቅድ ከተስፋ ባለፈ መሬት ላይ ለመውረድ ፈርጀ ብዙ ችግሮች ይኖሩበታል፡፡ አንዱ ምክንያት ደግሞ መንግስት ብቃት ያለዉን ባለሙያ ከመቅጠር ወደ ብሄር ኮታ በመዉረድ ለብሄር ብሄረሰቦች ያከፋፍላል፡፡ ይህም ቢሆን ሕወሃት/ኢህአዴግ ያለዉን ረጅም እጅ እየተጠቀመ በየሃገራቱ ያሉ አምባሳደሮች ሳይሆኑ ከታች የተቀመጡ የህወሃት ሰዎች መዘዉሩን ይዘዉታል፡፡
በመካከለኛዉ ምስራቅ ያሉ ኤምባሲ ሰራተኞች ለስደተኛዉ ወኪል መሆናቸዉን እረስተዉ በእጅ አዙር የጉዞ ወኪል በመክፈት በሴት እህቶቻችን ላብ በመነገድ ላይ ይገኛሉ፡፡ የኤምሲዎችን እርዳታ  ለመጠየቅ ወደ ኤምባሲዎች በር የሚሄዱ ኢትዮጵያዊያንን የቦንድ ግዢ እንዲያደርጉ ይጠየቃሉ በአንጻሩ ግን በኤምባሲያችን በር ላይ በአረብ ወሮ በሎች ሴት እህታችን ስትደፈር የወያኔ አምባሳደሮች የሚያዩበት አይን የሚሰሙበት ጀሮ አልነበቸዉም፡፡
ከሶስት አመት በፊት በዋሽንግተን የኤትዮጵያ ኤምባሲ ባልደረባ (ዲፕሎማት ለማለት ቃሉ ስለማይመጥኑ ነዉ) የነበረች አንዲት ኢት ዮጵያዊት እጽ በማዘዋወር በለንደን አዉሮፕላን ማረፊ እጅ ከከፈንጂ ተይዛ ዘብጥያ ወርዳለች ፤ ሰሞኑን እዚያዉ ዋሽንግተን በሰላማዊ ሰልፈኛ ኢትዮጵያዊያን ላይ ሶስት ጥይት ተኩሶ የሳተዉ ሰዉ ተጠርዞ ወደኢትዮጵያ እንዲመጣ ተደርጎል፡፡ ለካ መጠረዝ  በየተራ ለሁሉም ይደርሳል፡፡

ሕወሃት/ኢህአዴግ የያዘዉን የዘር ፖለቲካ ወደ ጎን ብሎ  ሁሉን አሳታፊ የሆነ መንገድ ቢከተል የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲዉ ብቻ ሳይሆን የአገሪቱ ዚጎችም በሚወዶት ሃገራቸዉ መስራት እና ማደግ ስለሚፈልጉ ለውጡ እጥፍ ድርብ ነዉ፡፡

Friday, September 12, 2014

ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ካልተካሄደ የከፋ ሁኔታ ሊከተል ይችላል!!

ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
በአንድ ሀገር የተረጋጋ የፖለቲካ ስርዓት ዘላቂ ሰላም መልካም አስተዳደርና የልማት ተነሳሽነት ሊኖር የሚችለው የህዝብ የስልጣን ባለቤትነት በተግባር ሲረጋገጥ ብቻ ነው፡፡ የህዝቡ የስልጣን ባቤትነት የሚረጋገጠውም ወቅቱን ጠብቆ በሚካሄድ ሁሉን አቀፍ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ነው፡፡ ይሁን እንጅ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅሜን ያሰጠብቁኛል፣በትክክል ያገለግሉኛል ይበጁኛል ብሎ ያመነባቸውን ተወካዮቹን በነጻነት በመምረጥ ዕውነተኛ የስልጣን ምንጭና ባቤትነቱን ለማረጋገጥ አልታደለም፡፡
AEUPየወያኔ/ኢሕአዴግ መንግስት ለጋሽ መንግስታትንና በአጠቃላይም ዓለምአቀፊን ማህበረሰብ ለማታለል እንደሚሞክረው አንድም ጊዜ ቢሆን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በህዝብ አልተረጠም፡፡ በእርግጥም በኢትዮጵያ ምድር ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ቢካሄድ ኖሮ ኢትዮጵያዊያን አገራቸውን ያሰገነጠለ የባህር በራችንን አሳልፎ የሰጠ ህዝብን በዘርና በቋንቋ የከፋፈለ፣ታርካችንንና የጋራ እሴቶቻችንን ያረከሰ በዘረኛ ፖሊሲው ትውልድን እያደነቆረ ብሔራዊ ስሜትን እየገደለ ያለን ቡድን ሊመርጡ የሚችሉበት ምክንያት አይኖርም፡፡ ለሀገሩ ቀናኢና ተቋርቋሪ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔ/ኢሕአዴግ መሪዎች ኢትዮጵያዊ ስሜት፣ሀገራዊ ፍቅርና ብሔራዊ ራዕይ እንዴለላቸው ከመጀመሪያ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ስለሆነም ወያኔ/ኢሕአዴግ መንግስት የፀጥታና የአፈና መዋቅሮቹን በማጠናከር ላለፉት 23 ዓመታት ኢትዮጵያን በኃይል ሲገዛ ቆይቷል፡፡ ወያኔ/ኢህአዴግ በአንድ በኩል የህዝብን የመደራጀት መብት በማፈን በሌላ በኩል “ጠንካራ ተቃዋሚ የለም”” እያለ ሲያፌዝ እንደነበረ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ከዚህም አልፎ ተቃዋሚዎች ህዝቡን በዙሪያቸው በማሳለፍ የሚያስችል አማራጭ አጀንዳ እንደሌላቸው ሲነገር ነበር፡፡
የወያኔ መሪዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ 85% የሚሆነው አርሶ አደር ህዝብ እንደሚደግፋቸው ያለምንም ይሁንታና ሀፍረት በመኩራራት ሲናገሩ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ያለው ሁኔታ እንደተለመደው ለመዋሸት የሚያመች አይደለም፡፡ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ በመላ ሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ህዝብን አደራጅቶ በመንቀሳቀስ ላይ ሲሆን በተለይ አርሶ አደሩ ህዝብ በወያኔ/ኢሕአዴግ አገዛዝ ላይ ያለውን የመረረ ተቃውሞ በተግባር አረጋግጧል፡፡ የመሬት ባለቤትነት መብቱን ተገፍፎ የወያኔ/ኢሕአዴግ ጭሰኛ በመሆኑ በድህነት እንዲማቀቅ የተፈረደበት የገጠሩ ወገናችን “ወያኔ ለፍርድ እንጅ ለምርጫ መቅረብ የለበትም” እያለ ነው፡፡ መኢአድ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ተካሂዶ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሽግግር እንዲደረግ የበኩሉን ታሪካዊ ኃላፊነት እየተወጣ ነው፡፡
በአሁኑ ሰዓት በየአካባቢው የተቀጣጠለውን የታቃውሞ እንቅስቃሴ በኃይል ለማፈን በገዢው ፓርቲ ካድሬዎችና ታጣቂዎች በኩል የተቀናጀ እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡ ሁኔታው ደርግ በውድቀቱ ዋዜማ ማንኛውም ታጣቂ ነጻ እርምጃ እንዲወስድ በግልጽ ካወጀው ጋር ተመሳሳይ አለው፡፡ በተለይ የመኢአድ አባላትና ደጋፊዎች በግልጽ ተኩስ ይከፈትባቸዋል፡፡ በየምክንያቱ ይከሰሳሉ ተይዘው ይታሰራሉ፣ ይደበደባሉ ከአቅም በላይ የሆነ የገንዘብ ቅጣት ይጣልባቸዋል፡፡ መሬታቸውን ይነጠቃሉ ንብረታቸውን ይዘረፋሉ፣ የቤታቸው የጣሪያ ቆርቆሮ ተገፍፎ ይወሰዳል ከዕድርና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች እንዲገለሉ ይደረጋሉ ቤተ-ክርስቲያን ገብተው እንዳያስቀድሱ ይከለከላሉ በምግብ ለስራ ለፍተው የሚያገኙት የእርዳታ እህል ይከለከላሉ ቤተሰቦቻቸው ጋር በሰላም በተገኙበት በውድቀት ሌሊት ተኩስ ይከፈትባቸዋል፡፡ ቤታቸው ይቃጠላል፡፡ ንብረቶቻቸውና የቤት እንስሳቶቻቸውም አብረው ይቃጠላሉ፡፡ በየደረጃው የሚገኙ የፍትህ አካላትም ሕግና ስርዓትን እንዲሁም ስብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የማስከበር ኃላፊነታቸውን ዘንግተው ለገዢው ፓርት የአፈና አገዛዝ ዋነኛ መሳሪያ እየሆኑ ነው፡፡ የተለያዩ ግፍና በደል የሚፈጸምባቸው አባሎቻችን የመክሰስ ዋስ የማቅረብ ለሌሎች ዋስ የመሆን መብቶታቸውን በፍትህ አካላላቱ እየተነፈጉ ነው፡፡
ከዚህም በላይ የመኢአድ አባላት በቅጥር ነፍ-ገዳዮች እንዲደበደቡ እንዲገደሉ ቤታቸው እንዲቃጠል ንብረታቸው እንዲዘረፍ ሚስቶቻቸው ሴት ልጆቻቸው እንዲደፈሩ እየተደረገ ነው፡፡ በአጠቃላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍና እጅግ ዘግናኝ ትዕግስት አስጨራሽና ሕዝቡን ለአመጽ የሚያነሳሳ በመሆኑ መፍትሄ ካልተፈለገለት ከማንም ቁጥጥር ውጭ የሆነ ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ከወዲሁ መታወቅ አለበት፡፡ መንግስት ከዚህ በፊት እንደሚያደርገው ሁኔታው በጠመንጃ ኃይል ለመቆጠጣር የሚያስብ ከሆነ ግን ለሚፈጠረው እሰከፊው ሁኔታ ተጠያቂው ራሱ የወያኔ/ኢሕአደግ መንግስት ነው፡፡ ማንም ወገን ሊገነዘበው የሚገባው አንገቢጋቢ ጉዳይ ቢኖር ሀገራችን ኢትዮጵያ እጅግ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሚትገኝ መሆኑ ነው፡፡
በመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደሚነገረን ሳይሆን በሀገራችን ድህነት ስራ አጥነት ረሃብና በሽታ ተንሰራፍቷል፡፡ በዚህ ላይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በርካታ ውስብስብ ችግሮች እየተፈጠሩ ነው፡፡ በተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎችና ብሔረሰቦች መካከል ግጭት ተፈጥሯል፡፡ ህይወት ጠፍቶል፡፡ ህዝብ ተስድዶል፡፡ በአጠቀላይ በየአካባቢው ሰላም ደፍርሶ ህዝብ በፍርሃትና በጥርጣሬ የሚታይበት ሁኔታ ተፈጥሮዋል፡፡ መልካም አስተዳደርና ፍትህን ማስፈን ያለበት መንግስት በየአካባቢው ሽብርና ፍርሃትን እያነገሰ ነው፡፡ ከዚህ አስፈሪ ቀውስና ውጥረት ለመውጣት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ/ በመጭው ዓመት ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ተካሂዶ ሰላማዊና ዴሞክራሲየዊ ሽግግር ይደረግ ዘንድ
1. ለተቃዋሚ ፓርቲ አባሎችና ደጋፊዎቻቸው የደህንነት ዋስትና እንዲሰጥ
2. የምርጫ ህጉ እንዲሻሻል
3. የምርጫ ቦርድ እንደገና እንዲዋቀር
4. በምርጫው ሂደት ውስጥ ነጻና ገለልተኛ ታዛቢዎችና ተቆጣሪዎች እንዲኖሩ
5. ለተቃዋሚዎች ለምርጫ የሚመደብ በጀት እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ
6. ሁሉም ተወዳዳሪ ፓርቲዎች በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዕኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማለት ከዚህ በፊት ያቀረብናቸው ጥያቄዎች በአስቸኳይ ተገቢ መልስ እንዲያገኙና በአካባቢው የህዝብን ተቃውሞና ጥያቄ ለማፈን በተለይ ደግሞ በመኢአድ አባሎችና ደጋፊዎች እየተፈጸመ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ሰቆቃ እንዲቆም አበክረን እንጠይቃለን፡፡ በመጨረሻ የወያኔ/ኢሕአዴግ መንግስት የያዘውን አደገኛ አካሄድና ግትር አቋም በማስቀየር ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ተካሂዶ በአገራችን የተረጋጋ የፖለቲካ ስርዓትና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ለሚከተሉት ወገኖች ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ፣ በኢትዮጵያ የተረጋጋ የፖለቲካ ስርዓት ሊሰፍን የሚችለው ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሲካሄድና የህዝብ የስልጣን ባለቤትነት ሲረጋገጥ ብቻ ነው፡፡
ወያኔ/ኢሕአዴግ ግን ከህዝብ ይሁንታና መልካም ፈቃድ ውጭ በጠምንጃ ኃይል አስገድዶ ዘላለም ሊገዛን ይፈልጋል፡፡ ገዢው ፓርቲ ስልጣን ላለመልቀቅ በሚፈጥረው ውጥረት ሀገራችን አሁን ካለችበት አሳሳቢ ሁኔታ ወደ ባሰ ቀውስ እንዳትገባ በተቀናጀ በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ትግል ወያኔ/ኢሕአዴግ የያዘውን ፀረ ኢትዮጵያ አቋም ለማስቀየር መላው ህዝባችን ከመኢአድ ጎን እንዲሰለፍ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡ ለወያኔ/ኢሕአዴግ አባላት፣ የደርግን አገዛዝ ለመገርሰስ በተካሄደው የትጥቅ ትግል ምን ያህል ህይወት እንጠፋና ምን ያህል የሀገር ንብረት እንደወደመ ሁላችን የምናውቀው ነው፡፡ ሆኖም ግን ያን ያህል ህይወት የተገበረበት እና የሀገር ሀብት የወደመበት እህል አስጨራሽ ትግል ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያ ህዝብ ያስገኘውን ፋይዳ አብረን እያየን ነው፡፡ የወያኔ/ኢሕአዴግ መሪዎች ሀገራችንን በማስገንጠል እና የባህር በራችንን አሳልፎ በመስጠት እንዲሁም ህዝባችንን በዘርና በቋንቋ በመከፋፈል የደገሱልንን ጥፋት ዛሬም ሁላችንም እየተቋደስነው ነው፡፡ አሁንም ቢሆን እነ አቶ ኃ/ማርያም እየተወዛወዙ ወደ ባሰ ጥፋትና ቀውስ እየመሩን ነው፡፡
በመሆኑም እያንዳንዱ የገዢው ፓርቲ አባል በጊዜያዊ ጥቅም እና የስልጣን ፍርፋሪ ሳይደለል ስለታገሉበት ዓላማ እና አገሩ ስላለችበት ሁኔታ ቆም ብሎ ማሰብና የመሪዎቹን የጥፋት እርምጃ በመግታት ኢትዮጵያዊነቱን ማስመስከር ይጠበቅበታል፡፡ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በአሁኑ ሰዓት በመንግስት ስም እየተወሰደ ያለው አቋም ሀገራችንን ወደ ከፋ ምስቅልቅልና የፖለቲካ አለመረጋጋት የሚወስድ ነው በመሆኑም የመንግስት ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነውና ጥያቄያችንን በቀጥታ የቀረበለት የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በዚህ አንገብጋቢ ጉዳይ ላይ በጥልቀት በመምከርና ገምቢ አቋም በመውሰድ ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ በኢትዮጵያ ህዝብ ስም እናሳስባለን፡፡ ለመከላከያ ሰራዊት አባላት ወያኔ/ኢሕአዴግ ህዝባዊ መሰረቱን አጥቶ ህልውናው በታጠቀው ክፍል ድጋፍ ላይ ብቻ የተንጠለጠለ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ የወያኔ/ኢሕአዴግ መሪዎች የህዝብን ስብዓዊና ዴሞክራሲየዊ መብቶች ለመርገጥና የአፈና አገዛዛቸውን ለመቀጠል የሚተማመኑት በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ግን የመከላከያ ሰራዊትም መሰረታዊ ተልዕኮ የሀገርን አንድነት፣ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት ማስጠበቅ መሆኑን ተገንዝቦ የገዥው ፓርቲ መሳሪያ ባለመሆን ህገ-መንግስታዊና ታርካዊ ኃላፊነቱን መወጣትና የህዝብ ወገናዊነቱን ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡
አንዲት ኢትዮጵያ ለዘላላም ትኑር
28/12/2006 ዓ/ም
- See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=1549#sthash.3dYmhqWV.DKnTcWeJ.dpuf

Tuesday, August 12, 2014

ኢህአዴግ ፣ እኛ እና ምዕራባዊያን (አብራሃም ለቤዛ)



Praising the traitor!!!
ባለራዩ  መሪ ፣ባለራዩ መሪ ፣ ዛሬ ድረስ የሚደመጥ የካድሬዎች የአፍ ማሞሻ ሀረግ ነዉ ፡፡  ከዚያማ ሌጋሲ ምናምን ፣ የማይሰቀጥሉት ነገር እንደሌለ ይነግሩን ነበር ፣ አሁን ድረስ ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ጭምር የሚሉት ነዉ፡፡
ሌጋሴ ወደ አማርኛ ስንገለብጠዉ ቀሪ መታዎሻ  ግለታሪክ የእኔም ፣ የአንቺም  በአጠቃይ የአገር መሪ የነበረ ብቻ ሳይሆን የተራዉ ሞችም ይኖረዎል፡፡ ዎናዉ ጉዳይ ምን አይነት ቀሪ መታዎሻ ታሪክ ጥለን አለፍን ነዉ፡፡
አቶ መለስ ዜናዊ  ምን  አይነት ቀሪ መታዎሻ ትተዉልን አልፈዎል ? ኢህአዴግን ከእሳቸዉ ዉጭ ማየት አንቺልም ለምን 21 ዓመት መርተዉታል፡፡ ኢህአዴግ በሙስና የነቀዘ ድርጅት ነዉ፣ አቶ መለስ በራሳቸዉ አንደበት ድርጅታቸዉ በሚመራዉ መንግስት ዉስጥ (ኢ.ፌ.ዲ.ሪ.) የመንግስት ሌቦች እንዳሉ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገልጸዉ ነበር፡፡
ኢህአዴጎች መጪዉ ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነዉ ይሉናል ምርጫ በመጣ ጊዜ፤ የኢህአዴጎች በመሬት ንግድ መክበር፤የፓርቲ ንግድ ማጦጦፍ፣ ከደሆች በተሰበሰበ ግብር በኢህአዲጋዊ ምቾት መኖር  ደሃዉ ኢትዮጵያዊ እነሱን ብቻ እንዲያኖኑር የተፈጠረ ስለሆነ ለእነሱ ብሩህ ነዉ፡፡
ኢህአዲጋዊ እስከሆንህ ድረስ እስከፈለገህ ትዘርፋለህ፣ የፈለግከዉንም መሬት በወረራ ትይዛለህ ፣ግፋ ቢል ኢህአዴጋዊነትህ ከቀነሰ በወረራ የያዝከዉን መሬት እንድትመልስ ይደረጋል፡፡ አንተ ላይ አንዳች ህጋዊ እረምጃ መዉሰድ ሌሎችን ኢህአዴጎችን ማስበርገግ ስለሆነ በማስተማር ትታለፋለህ ፡፡
ከኢህአዲጎች አንዱ በነበሩት ሰዉ፣ በአቶ መለስ ዜናዊ የበኩር ልጅ ፣ ሰመሃል መለስ ዜናዊ ስም የተመዘገበ አምስት ቢሊዮን ዶላር ቼክ (የህዳሴ አባይ ግድብን በእኛዉ በኢትዮጵያዊያን ተጀምሮ  በእኛዉ በኢትዮጵያዊያን የሚያስጨርስ ገንዘብ ያህል) በዉጭ አገር ባንክ እንደተንቀሳቀሰ ዶ/ር መኮንን ወንድሙ የተባሉ ኢትዮጵያዊ ለእንግሊዝ ምክር ቤት አቤት ማለታቸዉ የአደባባይ ሚስጢር ነዉ፡፡ ይህ ጉዳይ ልማተዊ ነኝ ለሚል መንግስት አሳስቦት ማስተባበያ ሊሰጥበት  የሚገባዉ ሲሆን  ጀሮ ዳባ ልበስ መባሉ ያስገርማል፡፡
ዕራብያዊያን  ለደሃ አገራት ከሚሰጡን እርዳታና ብድር በላይ ከደሃ አገራት ሙሰኛ ባለስልጣናት  የሚመዘበሩትን ሃብት በታማኝነት በማስቀመጣቸዉ የበለጠ ደሃ አገራት እንዲቆረቁዙ፣ ዜጎቹም ከሰዉ በታች እንዲኖሩ ምክንያት ሁነዎል፡፡ ለዚህ ደግሞ እንደምሳሌ ስዊዘርላንድን (Switherland) ብንወስድ ካላት አመታዊ ምርት (GDP) አንጻር ከከፍተኛ ለጋሽ አገሮች ተርታ የምትመደብ ሲሆን በተቃራኒዉ እንደዚህ የምትጨነቅላቸዉ አገራት ዜጎች ገንዘብ ተዘርፎም ሲመጣ አንጀቶ አይጨክንም፤ በሚስጢር በባንኮቾ ታስተናግዳለች፡፡
ምዕራብያዊያን አገራት የዲሞክራሲ ስርዓት ቱርፋት ተጠቃሚዎች ቢሆኑም ለእኛ ለአፍሪካዊያን ግን የዴሞክራሲ ቱርፋት እንዲደርሰን እየረዱን አይደለም ፤ ምናልባትም እኛ አፍሪካዊያን ለአቅመ መብላት እንጂ ለአቅመ ዴሞክራሲ የደረስን አይመስላቸዉም፡፡ በእርግጥ እኛ አፍሪካዊያን (ኢትዮጵያዊያን) ሰልፋችንን ማስተካከል አለብን፡፡ ለዴሞክራሲ የሚደረግ ትግል ከምእራብያዊያን ጉልበት አያገኝም ፤ ዎናዉ ጉልበት ያለዉ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ነዉ፣ነገር ግን ልምድ ከነሱ መቅሰም ይቻላል፡፡
ምዕራብያዊያን ጥቅማቸዉን እስከተጠበቀ ድረስ ሰልፋቸዉን አይለዉጡም ፣ ነገር ግን  ህዝብ ከተነቃነቀ ፣ ህዝቡ የድል ችቦዉን ሊለኩስ ሲዘጋጅ በቅጽበት አቆማቸዉን ይለዉጣሉ፡፡ እዚህ ላይ አንድ ምሳሌ ማንሳት ይቻላል፡፡ የፈረንሳይ መንግስት በወዳጁ የቤንአሊ የቱንዚያ መንግስት ላይ በ2011 ዓ/ም (እ.አ.አ) ሕዝባዊ አመጽ በተነሳበት ሰዓት ቤንአሊን ለመታደግ አድማ በታኝ ተሽከርካሪዎች ለመላክ በተዘጋጀበት ሰዓት ፋታ የማይሰጠዉ ሕዝባዊ አመጽ በተቀጣጠለበት ሰዓት ቤንአሊ ሆየ እንደለመዱት በአዉሮፕላናቸዉ ወደ ፈረንሳይ ሲበሩ ምእራባዊቶ ፈረንሳይ የአየር ክልሎን ዘግታ  እንትንህን ላስ ብላቸዎለች፡፡
የዚህች መልዕክት አላማ ትግላችንን በህዝብ፣ለህዝብ፤ከህዝብ ብቻ ከሆነ አምባገነኑን የኢህአዴግ ስርዓት አሰወግዶ በምትኩ ሰፊ መሰረት ያለዉ ህዝባዊ ስርዓት ማምጣት እንደሚቻል ለመጠቆም ያህል ነዉ፡፡ ቸር እንሰንብት፡፡


ለአስተያየተዎ (anethiopian@yahoo.com)


ኢትዮጵያንና ህዝቦቾን እግዚአብሄር ይባርክ!!!!

Sunday, July 20, 2014

ኢትዮጵያዊነትን መረዳት ወይስ በተስፋፊዎች ቅዠት መነዳት(አብራሃም ለቤዛ)


ኢትዮጵያ በረዥም ዘመን ታሪኳ አባጣና ጎርባጣዉን የታሪክ ምንጣፍ አልፋ ዛሬ ደርሳለች፡፡  ይህን የታሪክ አካላችንን ኢትዮጵዊያን ከፊሉን በንጉሳዊያን ዜና መዎዕል እንዲሁም ሌሎች የታሪክ ድርሳናትን አቆይተዉናል፡፡ ከኢትዮጵያዊያን በተጨማሪም ኢትዮጵያን የጎበኙ አሳሾችም ሆነ ሚሺነሪዎቸ ስለኢትዮጵያ ታሪክ  ጥናቶቸን አድርገዎል፡፡  ነገር ግን ከምእራብያዊያን መስፋፋት ጋር በተገናኘ ከፊሎች የዉጭ ሃገር ጸሃፊዎች የኢትዮጵያን ህዝብ አንድ ያልሆነ ህዝብ የባሪያ ፍንገላ የሚከናወንበት በሃገሩ ንጉሶችችቆና የሚደርስበት የእራሳቸዉን ሃገር በወረሪነት በመምጠት ሊታደጋቸዉ እንደሚገባ ወትዉተዎል፡፡  ይህ የታሪክ ትርክት እዉነትነት ቢኖረዉ እንኳን በጸሃፊዎች ድብቅ አጀንዳ ምክንየት ተጋኖና ተዘብቶ እንደሚቀርብ መረዳት አያዳግትም፡፡
ታዲያ እነዚን የመሳሰሉ የታሪክ ጸሃፊዎች የጻፉትን የታሪክ መጸሃፈት በመያዝ ነዉ አንዳንድ ልሂቃን እንወክለዎለን የሚሉትን ህዝብ ሲያወናብዱት የሚታዩት፡፡ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያሉ የተለያዩ ዘዉጌ ማህበረሰቦችን የተለያዩ እና እራሳቸዉን የቻሉ ብሄራዊ ህዝቦች በማድረግ ለዘመናት በጋራ የኖረዉን ህዝባችንን እያመሱት ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵዊያን በረዥም ዘመን ታሪካቸዉ በተለያዩ በጎም ሆነ አጥፊ መንገዶች ተጉዘዉ የተቀላቀሉ ህዝቦች ናቸዉ፡፡ ቢያንስ በነዚህ ሁለት ምክንያቶች የተዎሃድን ህዝብ መሆናችንን ማየት ይቻላል፡፡  
ጦርነት
የኢትዮጵያ ታሪክ የጦርነት ታሪክ እንደሚበዛዉና ኢትዮጵያዉያንም ሰላም ያገኙበት ዘመን የቅንጦት ዘመናቸዉ እንደነበር አንጋፋዉ የኢትዮጵያዊነት አርአያ ፕሮፌሰር መስፍን በመጽሃፋቸዉ (መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ) ይገልጻሉ፡፡  ኢትዮጵያዊያን አንድ ጊዜ እርስ በእርሳቸዉ ሌላ ጊዜ ከወራሪዎችና ከተስፋፊዎች ጋር የሚያደርጎቸዉ ጦርነቶች የሰላም ህይወትን ቅንጦት እንዲሆን አድጎታል ፡፡ በእርስ በእርስ ጦርነቶች ጊዜ በጦርነት ያሸነፈዉ ወገን ተሸናፊዉን በምርኮ በመያዝ ምርኮኛዉ ካቆየ በሆላ የራሱን ባህልና ቋንቋ እንዲላመድ አድርጎ የጎሳዉ አካል አድርጎ ይቀበለዎል፡፡ የቅርቦቹን ነገስታት ታሪክ ከተመለከትን ደግሞ በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱባቸዉን ተቀናቃኝ የልዑላን ቤተሰብ ለማለዘብ ሴት ልጆቻቸዉን በመስጠት ተቀናቃኞቻቸዉን ታማኝ ለማድረግ በሚፈጥሩት መላ ኢትዮጵያዊያን የመቀላቀል እድላቸዉ ሰፊ ነዉ፡፡ አንድ የንጉስ ልጅ ወደ ተቀናቃኙ መሳፍንት ስትሄድ ደንገጡሮቾን ጨምራ ብዙ ጋሻጃግሬዎች እንደሚኖራት ጥርጥር የለዉም ታዲያ  ይህ ሁሉ የስኮዱ አባላት የቀቅልቅሉ አካል ናቸዉ፡፡
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያዊያን እርስ በርሳችን ተናቁረን ተናቁረን የዉጭ ወራሪ ወይም ተስፋፊ ሲመጣ በጋራ የመከትንባቸዉ አጋጣሚዎች ከታሪካችን ማህደር ይመዘዛሉ፤ ይህ ማለት ደግሞ በየጎበዝ አለቃዉ የሚመራዉ የኢትዮጵያ ጦር ረዥሙን የዘመቻ ጉዞ ሲያካሄድ በሚንቀሳቀስባቸዉም ሆነ ስንቁን ለመቆጠር በሚያርፍባቸዉ አካባቢዎች ከአካባቢዉ ህዝቦች ጋር የመቀላቀል እድሉ ሰፊ ነዉ፡፡ ይህ ጉዳይ ክብደት የሚሰጠዉ ኢትዮጵያዊያን በተደጋጋሚ ወረራዎች ይሞከሩብን ስለነበረ ነዉ፡፡
በቅርብ ጊዜ ታሪካችን እንኳን ብንመለከት በኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት መቆያነት ያገለገሉት አዘዞ (ጎንደር) አሰብና ነገሌ ቦረናን የመሳሰሉ ቦታዎች የኢትዮጵያዊያን ቅልቅልነት የሚያሳዩ ቦታዎች ናቸዉ፡፡
ገበያ
የኢትዮጵያ ወዳጅ የሆነዉ ተማራማሪዉ ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን ታላቋ ኢትዮጵያ በሚለዉ መጽሃፋቸዉ ኢትዮጵያ የህዝቦችና የባህሎች ሙዚየም መሆኖን ጠቅሶ ኢትዮጵያዊያን ህዝቦች በጋራ የሚወራረሶቸዉ በጣም ብዙ ነገሮች በመኖራቸዉ ኢትዮጵያዊያን የተለያዪ ህዝቦች ሳይሆኑ አንድ እንደሆኑ የቋንቋ፤ ባህልና እሴቶች ዉርርሶችን እያጣቀሱ ያብራራሉ፡፡ ኢትዮጵያዊያን አሞሌ ጨዉ፤ ቡና፡ ሸማ፡ እደ ጥበቦች፡ የእርሻ ቁሳቁሶችና የመሳሰሉትን  በሲራራ ነጋዴዎቻቸዉ አማካኝነት በጋራ የሚገበያዩባቸዉ ትላልቅ ገበያዎች እንደነበሩ ይጠቅሳሉ፡፡ በእነዚህ ትላልቅ ገበያዎች ለመሳተፍ  ከኢትጵያ ሰሜን ጫፍ እስከ ደቡብ ጫፍና ከምዕራብ ጫፍ እስከ ምስራቅ ጫፍ ሁሉም ያለዉን ይዞ የሌለዉን ለማምጣት ስለሚሄድ ሃገረዊ ቅልቅል ለመፈጠሩ አንዱ ማሳያ ነዉ፡፡