Followers

Sunday, October 15, 2023

ኤርትራና ሲንጋፖር -አብራሃም ለቤዛ

 

 

ኤርትራና ሲንጋፖር
አብራሃም ለቤዛ
>><<>><<>><<>><<>><<>><<>><<>><<>><<>><<>>><<>><<>><<>><<>><<>><<
ኤርትራና ሲንጋፖር
አብራሃም ለቤዛ

ኤርትራ ከሲንጋፖር ጋር ለመተረክ የፈለግኩት ከሰሞኑን የኤርትራ የተባበሩት መንግስታት ተቀማጭ አማባሳደር ከሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስተር  Mr. Yap Ong Heng ጋር ተገናኙና ተወያዩ የሚል ዜና ነው፡፡  ነገር ነገር ያነሳዎል እንዲሉ ለመተረክ የፈለግኩት ስለሁቱ አገሮች ግንኙነት ሳይሆን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር እንሆናለን ይል ስለነበረው የኤርትራዊያን ቅዠት ነው፡፡

የኤርትራ መንግስት ከኢትዮጵ ለመገንጠል በሚያደርገው ጥድፈት ዋዜማ ኤርትራን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር እናደርጋታል ይል ነበር፡፡  የየደቡብ ምስራቅ ኤሺያ አገሮች በአጭር ጊዜ ከድህነት ስለወጡ ለብዙ የአፍሪካ አገሮች መቅኛ ነበሩ፡፡  ፈጣን እድገትና ልማት ግን ትክክለኛ  የፖሊሲ አቅጣጫ በመያዝ የሚመጣ እንጂ በማለም ብቻ የሚሆን አይደለም፡፡  የኤርትራዊን የምስራቅ አፍሪካ ሲንጋፖር የመሆን ምኞት የመጣው ራሳቸውን ከሌላው ሀባሻ የኢትዮጵ ህዝብ እንዲሁም ከትግሬ ወንድሞቻቸው ለይተው ማየታቸው ነው፡፡ የ60 ዓመት የጣሊያን ቅኝ ገዢ ፖሊሲ በኤርትራዊያን ላይ ይኸ አስተሳሰብ እንዲጫን አድረጎል፡፡ ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ “Ethiopia and Eritrea- The Federal Experience”  በሚለው ጥናታዊ ፅሁፋቸው ኤርትራዊያን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዳግም የሄዱበት መንገድ እኛ የተለየን ነን ፤ ከሃበሻ እኛ የሰለጠንን ነን፤ እኛ ከተገነጠልን በፍጥነት እንበለፅጋለን የሚለው አስተሳሰብ ስለሰረፀባቸው ነው ይላል፡፡

የሆነው ግን ኤርትራ የአፍሪካ ሲንጋፖር ሳይሆን የአፍሪካ ሰሜን ኮርያ ሆነ፡፡ የሃበሻ ምቀኝነት እንዲሉ ለዚህ ደግሞ የወያኔ ኢተዮጵያ ኤርትራን በማሳጣት ትልቅ አስተዋፅኦ አድርጋለች፡፡

የደቡብ ምስራቅ ኤሽ አገሮች ሲንጋፖር ፤ ማሌዥያ፤ ቬትናም፡ታይላድ ፤ኢንዶኔዢያና ፊሊፒንስ ሲሆኑ ፤ በአጭር ጊዜ ከድህነት በመውጣታቸው ምክንያትም የኤሽያ ታይገር የሚል የዳቦ ስም ወጥቶላቸዋል፡፡  የወያኔዎ ኢትዮጵያ ልማታዊ መንግስትን በመከተል የደቡብ ምስራቅ ኤሽያ አገሮች መንገድ እከተላለሁ ብትልም፤  ነገር ግን የኢትዮጵያ ፖሊሲ በጎሳ ፖለቲካ ፤ የጋራ መግባባት የሌለው ፖለቲካ ሃይል እና በሙስና የተጨማለቀ ፖለቲካ ሃይል የተተበተ ስለሆነ የደቡብ ምስራቅ ኤሽያ አገሮችን ፈለግ መከተል አልቻለችም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለራሷ የአፍሪካ ላይዮን የሚል የዳቦ ስም አውጥታለች፡፡ ለከታታይ 14 ዓመት (2005-2019)  በሁለት ዲጂት ያደገ ኢኮኖሚ ባለቤት የሚል የተለመደ የወያኔዎች የአፍ ማሞሻ ጥቅስ ነበር፡፡

ፅንፈኛው ጃ-War  መሃመድ   የኦሮሞ ፖለቲከኛም በሲንጋፖር ኢኮኖሚ እምርታ እንደሚማረክና ሲንጋፖር እየተማረ

የሲንጋፖርን እድገት እናዳጠናዉም በተደጋጋሚ ይገልፃል፡፡ ችግሩ የሲንጋፖርና የደቡብ ምስራቅ ኤሽያ አገሮች ሲንጋፖር አገሮች መመንደግ ሳይሆን እነሱ የሄዱበትን  እኛ እንዳንሄድበት  ራሳችንን አድርገናል፡፡ የእኛ መንገድ ማለት በህገመንግስታችንም ሆነ በኢኮኖሚ ፖሊሲያችን ኢትዮጵያዊነት በዜጋነት እንዲደራጁ አንፈቅድም፡፡  የብሄር ፖለቲካ ይዘን እንደ ዝንጀሮ መንጋ ባለች ሃብት (ክምር) ላይ ሰፍረን መበዝበዝ እንጂ ምርታማነትና ዕድገትን አናመጣም፡፡

ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ እንዲሉ የአፍሪካ ፖለቲከኞች ፊት ለፊት ያገጠጠ ፖለቲካ ችግራቸውን ከመጋፈጥ ይልቅ የጦስ ዶሮ መፈለግ ይዘዎል፡፡ አዎ ላላማደጋችን ወደብ-አልባ አገር መሆናችን ትለቅ አስተዎፅኦ አለው ነገር ግን አሁን ያለንበት ተጨባጭ ሁኔታ ሌላ የበለጠ አሳሳቢ ጉዳያችንን መፍታት አልቻልንም፡፡ አገርን ሰላም ማድረግ መንግስት አልቻለም፤ ዜጎች በሰላም ወጥተው መግባት አልቻሉም፡፡

ብልፅግና መራሹ ፤ የኦሮሞ ፅንፈኞች ከዚህ መማር ቢችሉ ኢትየጵያዊያንን በአንድ ማስተባበር አለባቸው፡፡ ብቻቸውን ግን ቀይ ባህር ፤ ህንድ ውቅያኖስ የሚሉት አያዋጣውም፡፡ ሻብያና ኦነግ ከ30 ዓመት በፊት በአንድ ሰርተዎል ፤ አሁን ደግሞ አንዱ የጣለውን መንገድ አንዱ እያነሳ ባለህበት እርገጥ ሆኖል፡፡

Wednesday, August 30, 2023

የኦሮሞ ብሔርተኞች ተቃርኖ [Hypocrisy]! – አቻምየለህ ታምሩ

 የኦሮሞ ብሔርተኞች ተቃርኖ [Hypocrisy]! – አቻምየለህ ታምሩ

በኢትዮጵያ ምልሰት ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራችውን የኦሮሞ ጀግኖች እንደ ኦነግ ያዋረደ ድርጅት የለም። በቤተ ኦነግ የጀግኖቹ ጀግና፣ የራሶቹ ራስ የራስ ጎበና ስም ስድብ ነው። እኛ ከፍ ስናደርጋቸው እነሱ ዝቅ ሲያደርጓቸው የኖሩትን የኢትዮጵያ ጀግኖች እፍረተ ቢሶቹ ኦነጋውያን ዛሬ ስማቸው ሳይጠራ የኖሩ ኦሮሞዎች አድርገው ለመተረክ ይቃጣቸዋል። ብሔርተኞቹ ነውረኞች ስለሆኑ በንጉሡ ስር የአድዋ ዘመቻ ጠቅላይ ጦር አዛዥ የነበሩትን የራስ መኮነንን መታሰቢያ ሐውልት በቅርቡ በሐረር ከተማ አናታቸው ይፍረስና ማፍረሳቸውን እንኳ የረሳነው ይመስላቸዋል።

ለመሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የኦሮሞ ጀግኖችን አስተዋጽኦ ከኦነግ በላይ የረሳና ያዋረደው ማነው? ከኦነግ በተጨማሪ የኦነግ ፕሮግራም አቀንቃኝ ብሔርተኞች አይደሉምን? አገራቸው ያቆመችላቸውን ሐውልትና ስም የደመሰሱ እነዚህ ነውረኞች አይደሉምን?

በክርስትና ሃይማኖት የቤተ ክርስቲያን መሰረት የሚባሉ አራት ጉባኤዎች አሉ። ቤተክርስቲያን የፀናችው በነዚህ አራት ጉባኤዎች ነው ተብሎ በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ይታመናል። ይህንን framework በመጠቀም በ1927 ዓ.ም. ከዛሬ 84 ዓመታት በፊት የጎጃሙ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ራስ ጎበናን የኢትዮጵያን ምልሰት ካቆመው አራቱ ጉባኤ መካክል አንዱ ያደርገዋል። በወቅቱ የነበረው የመንፈስ ድክመት አገራችንን አደጋ ላይ ቢጥላት ኢትዮጵያ ምህርት ወይንም መዳን ታገኝ ዘንድ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ የጠራው የኢትዮጵያ ብርታት የቆመበትን የነራስ ጎበናን መንፈስ ነበር። እንዲህ ሲል. . .

አጥንቱን ልልቀመው መቃብር ቆፍሬ፣
ጎበናን ከሸዋ አሉላን ተትግሬ፤
ስመኝ አድሬአለሁ ትናንትና ዛሬ፣
ጎበናን ለጥይት አሉላን ለጭሬ፤
****
ተሰበሰቡና ተማማሉ ማላ፣
አሉላ ከትግሬ ጎበና ከጋላ፤
ጎበና ሴት ልጁን ሊያስተምር ፈረስ፣
አሉላ ሴት ልጁን ጥይት ሊያስተኩስ፤
አገሬ ተባብራ ካልረገጠች እርካብ፣
ነገራችን ሁሉ የእንቧይ ካብ የእንቧይ ካብ፤
***
[የኔ ራስ] ጎበና ከፈረስህ ጋራ ተነስ እንደገና፣
ትምህርት እንዲስፋፋ ጉልበት እንዲጠና፣
አራቱ ጉባኤ ይነሱልንና፣
መኮንን ደረሶ አሉላ ጎበና፣
አገራችን ትማር አሁን እንደገና፤
[የኔ ራስ]ጎበና ከፈረስህ ጋራ ተነስ እንደገና።

በዚህ የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ገድልና ጀብዱ ላይ የሸፈቱት ኅሊና ቢሶች ኦነጋውያንና የርዕዮታለም መንትዮቻቸው ናቸው። የእነ ራስ ጎበናና የተቀሩት የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞችን አገርና ታሪክ ለማፍረስ እነ ኦነግ ሞቃዲሾ ሲከትሙ፣ እነ ኢሕአፓ ወደ አሲምባ ሲኮበልሉ፣ እነ ሕወሓት ደደቡት ሲወርዱ የራስ ጎበናንና የሌሎችን ኢትዮጵውያን ጀግኖች አርበኞች ታሪክ ጠብቆ ያቆየው እንደ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ አይነቱ አማራ ነው።

ዐፄ ዮሐንስ ምንም እንኳ ጎጃምና ወሎን ቢጨፈጭፉም መተማ ላይ ሰማዕት በመሆናቸው አማራው የሚያከብራቸውን ያህል በፋሽስት ወያኔዎች ዘንድ ክብር የላቸውም። አማራው መተማ ዮሐንስ የሚል ከተማ በስማቸው ሲጠራ ፋሽስት ወያኔዎች ግን በባለሟላቸው በራስ አሉላ ስም የተሰየመውን ትምህርት ቤት የትግራይን ሪፑብሊክ ለመመስረት ደደቢት በወረደው መለስ ዜናዊ ስም ለውጠውታል።

የኦሮሞ ብሔርተኞች ከሰሞኑ የአድዋን ድል ዋነኞቹን የጦሩ አዛዦችን ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምኒልክንና እቴጌ ጠሐይቱን ትተው የኦሮሞ ጀግና ፈረሰኛ ወታደሮች ድል እንደሆነ አድርገው እየተናገሩ ናቸው። እንደሚታወቀው የአድዋ ጦርነት ጥሊያን የተጨፈጨፈበት ድል ነው። የኦሮሞ ብሔርተኞች እየነገሩን ያለው ይህንን የጥሊያን ጭፍጨፋ ያካሄዱት የኦሮሞ ፈረሰኛ ወታደሮች ናቸው የሚል ነው። ጥሩ። ይህንን የሚሉትን የኦሮሞ ብሔርተኞች አኖሌና ጨለንቆ ላይ ተካሄዱ ለሚሏቸው ጦርነቶች ተደረገ ለሚሉት ጭፍጨፋ ግን ኃላፊነቱን የዳግማዊ ምኒልክ ያደርጉታል።

በታሪክ ሞቅ ሲል በማንኪያ፤ ሲቀዘቅዝ በእጄ አይሰራም። በአድዋ ድል የኦሮሞ ፈረሰኛ ወታደሮች ከሆነ የአርሲና የሐረር «ጭፍጨፋ» የተባለውንም የፈጸሙት እነዚህ የአድዋ ድል ባለቤት የተደረጉት ጀግና የኦሮሞ ፈረሰኛ ወታደሮች ናቸው። ለአድዋው ድል ሲሆን እውቅናው ከሁሉ በላይ ለጀግና የኦሮሞ ፈረሰኛ ወታደሮች፤ እነኚህ ወታደሮች አርሲና ሐረር ባካሄዱት የማስገበር ዘመቻ ደረሰ ለሚባለው «ጭፍጨፋ» እና «ቅኝ ግዛት» ግን ተጠያቂው ዳግማዊ ምኒልክ ሊሆኑ አይችሉም!

«ሰውን ሲወዱ ከነንፍጡ እና ልጋጉ ነው» ይላል ያገሬ ሰው። በአድዋ ላይ የተመዘገበውን ድል ከሁሉ በላይ የኦሮሞ ጀግና ፈረሰኛ ወታደሮች የሰጠ አንድ ሰው፤ ከአድዋው ድል ጥቂት አመታት በፊት እነዚሁ የኦሮሞ ፈረሰኛ ወታደሮች በአርሲና ሐረር ያደረሱትን «ጭፍጨፋም» የራሱ ወገን የሆኑ ሰዎች ያደረሱት መሆኑን አምኖ ትክሻውን ደልደል በማድረግ መቀበልና ተፈጸመ ላለው ጭፍጨፋም ተጠያቂ ማድረግ ካለበት እነሱኑ ነው እንጂ ሌላ አካል ተጠያቂ ማድረግ የለበትም።

ስለዚህ ዛሬ የኦሮሞ ብሔርተኞች በአድዋው ድል እውቅና እየሰጧቸው ያሉት የኦሮሞ ፈረሰኛ ወታደሮች ከአድዋ ድል ጥቂት አመታት በፊት እነዚሁ የኦሮሞ ወታደሮች ሐረርና አርሲ ላደረሱት «ጭፍጨፋ» እና «ቅኝ ግዛት» ዳግማዊ አጤ ምኒልክ ተጠያቂ የሚሆኑበት አመክንዮ ሊኖር አይችልም! ስለሆነም ወይ የአድዋውን ድልም እንደ አኖሌውና ሐረሩ ጭፍጨፋ ሁሉ ለምኒልክ ተውት አልያም በነዚሁ አድዋ በዘመቱ የኦሮሞ ጀግና ፈረሰኞች የተካሄደውን የአርሲና የሐረሩ ጭፍጨፋ ያላችሁትንም እንደ አድዋው የጥሊያን ጭፍጨፋ ሁሉ ኃላፊነቱን በመውሰድ ተጠቃለሉትና ምኒልክን ለቀቅ አድርጓቸው  Otherwise it is pure hypocrisy to make such a sudden U-turn 213

Tuesday, June 6, 2023

በካራማራ ታንክ ማራኪው ጀግና ሻለቃ ባሻ አሊ በርኬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ (ካራማራ የኢትዮጵያውያን የድል ቀን (ዳግማዊ ዓድዋ) ጋዜጠኛ መአዛ መሀመድ)

       ካራማራ የኢትዮጵያውያን የድል ቀን (ዳግማዊ ዓድዋ) ጋዜጠኛ መአዛ መሀመድ








ካራማራ የኢትዮጵያውያን  የድል ቀን (ዳግማዊ ዓድዋ)

ጋዜጠኛ መአዛ መሀመድ
 
እንደ መግቢያ 
  በ1950ዎቹ መጀመሪያና አጋማሽ ላይ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነፃ የወጡባቸው አመታት ነበሩ ። የጣሊያን ሶማሊ ላንድና የብሪቲሽ ሶማሊላንድም በ1952 ነፃ ወጡና የሶማሊያን ሪፐብሊክ መሠረቱ ።
  ቀጥሎም ባለ 5 ኮከብ ያለው ባንዲራ አስተዋወቁ ። ትርጉሙም በኢትዮጵያ ፣ በኬንያ ፣ በጅቡቲ እና ሪፐብሊክ በመሠረቱት ሁለቱ ሶማሊላንዶች የሚገኝ መሬት የሶማሊያ ነው የሚል የታላቋ ሱማሊያ ህልም የሚያመለክት ነበር ።
  ከኢትዮጵያ ሉአላዊ መሬት ላይም አጠቃላይ ሐረርጌን ፣ ባሌን ፣ አርሲን ሲዳማንና ከፊል ሸዋን ለመጠቅለል የሚያስችል አዲስ ካርታ አዘጋጁ ።
  ጅቡቲና ኬንያ በቅኝ ግዛት ስር ስለነበሩ ለጊዜው እነሱን በመተው ነፃ ሀገር በነበረችው ኢትዮጵያ ላይ የተለያዩ የሰርጎ ገብ ጥቃቶችን ይፈፅሙ ጀመር ። ኦብነግና ኦነግን የመሣሠሉ ተገንጣይ ቡድኖችን በማቋቋም የእጅ አዙር ጥቃትን አፋፋሙ ።
  ሶማሌዎች በ1953 ዓ.ም. በኢትዮጵያ የተከሰተውን የታህሳስ ግርግርን ተከትለውና በ1956 ዓ.ም. ላይ ከደፈጣ ጥቃት ወደ መጠነ ሰፊ የወረራ ሙከራ አደረጉ ። ሆኖም በጊዜው ቀጠናውን ይጠበቅ በነበረውና በጀግናው ሌ/ጀ አማን ሚካኤል በሚመራው 3ኛው አንበሳ ክ/ጦር ክፋኛ ተመትቶ ተመለሡ ።
   በ1962 ዓ.ም. ወታደሩ ጀነራል መሀመድ ዚያድባሬ በመፈንቅለ መንግስት የሶማሊያን መንግስት በትረ ስልጣን ተቆጣጠሩ ። የታላቋ ሶማሊያ ህልማቸውንም በይፋ ገልፀው ወታደራዊ ዝግጅታቸውን አጧጧፉት ። የመንግስታቸው ርዕይቶ አለምም በይፋ ሶሻሊዝም መሆኑን አወጁ ።
  በውጤቱም ከሶቪየት ህብረት በገፍ ዘመናዊ መሳሪያ መታጠቅና ወታደራዊ ኃይላቸውን ለተከታታይ 7 አመታት ማፈርጠም ቀጠሉበት ። በውጤቱም 7 እግረኛ ክፍለ ጦር ፤ 600 ታንኮችን እና ሌሎች የያዘ 4 ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር እንዲሁም 70 አውሮፕላኖችን የያዘ ግዙፍ የአየር ኃይል ገነቡ ።
  በአንፃሩ ኢትዮጵያ ሌላ የታሪክ ሂደት ላይ ነበረች ። የየካቲት 1966ዓ.ም. አብዮት ተከትሎ ቀኃሥ ከዙፋን አውርዶ መስከረም 2 /1967 ዓ.ም. ስልጣን ላይ የወጣው ወታደራዊው ደርግ በበርካታ ጉዳዬች ተጠምዶ ነበር ።
  በሰሜን ነፍጥ አንስቶ የሚታገለው ሻእቢያና ጀብሃ ከአሥመራ ፣ ከፊል ምፅዋና ባሬንቱ በስተቀር ቀሪውን የኤርትራ ክ/ሀገር ተቆጣጥረው ነበር ።
  ኢዲዩ በጎንደር ፤ ህወኃትም በትግራይ መንግስትን በመፋለም ላይ ነበሩ ። በመሃል ሀገርና በሌሎች አከባቢዎችም ኢህአፓና ደርግ በነጭ ሽብርና በቀይ ሽብር ደም ይፋሰሱ ነበር ።
  ተቀናቃኝ ሀይሎቹም በመንግስት ላይ የሚፈፅሙት ጥቃት አልበቃ ብሏቸው ሶማሊያ የምታደርገው ጦርነት ልክ ነው ፤  አድሃሪ ጦርነት የሚያደርገው ደርግ ነው በማለት ሻእቢያ ፣ ህወኃት ፣ መኢሶን ፣ ኢህአፓ ፣ ኦነግ እና ጀብሃ የፕሮፓጋንዳ ድጋፋቸውን ለሶማሊያ ይሰጡ ነበር ።
በውጤቱም ኢትዮጵያ እጅግ ተዳክማ ነበር ።
    በአጠቃላይ ዚያድባሬ ያንን ሁሉ ግዙፍ ወታደራዊ ዝግጅት ሲያደርግ የኢትዮጵያን የመንግስት ስልጣን የያዘው ደርግ ግን ከንጉሱ የተቀበለው 4 ክፍለ ጦሮች ብቻ ነበሩት ።
  እነርሱም 1ኛ ክ/ጦር (ክቡር ዘበኛ ) ፤ 2ኛ ክ/ጦር ኤርትራ የነበረው ፣ 3ኛ ክ/ጦር ምስራቅ (ኦጋዴን) የነበረው እና 4ኛ ክ/ጦር ደቡብ ነገሌ/ቦረና የነበረው ናቸው ። ከነዚህ ውጭ ተጨማሪ ኃይል አሠልጥኖና አስታጥቆ ወደ ሰራዊቱ አልጨመረም ነበር ።
   የጦርነቱ ውጥረት እያየለ ሲመጣ የተለያዩ የማሸማገል ጥረቶች በተለያዩ አካላት ቀጥለው ነበር ። የመጨረሻው የፊደል ካስትሮ ደቡብ የመን ኤደን ላይ ለማሸማገል ያደረጉት ጥረት በዚያድባሬ እብሪት ምክንያት ከሸፈ ።
  ፊደል ካስትሮም በዚያድባሬ መጠን ያለፈ ንቀት እጅግ ተቆጡ ፤ በአለማቀፍ ህብረተሰባዊነት መርህ መሠረትም ኢትዮጵያንም ማገዝ እንዳለባቸው ወሰኑ ። እያንዣበበ ያለው የመወረር አደጋ ያሰጋቸው የወቅቱ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት መንግስቱ ኃ/ማርያም ሚያዚያ 4 ቀን 1969 ዓ.ም. በብሔራዊ የቴሌቭዢን ጣቢያ ብቅ ብለው ታሪካዊውን የእናት ሀገር ጥሪ መልእክት ለህዝባቸው እንዲህ በማለት አስተላለፉ ። ሀገርህ ፣ ህልውናህን እና አብዮትህን አድን ፤  ተነስ ! ታጠቅ ! ዝመት ! እናሸንፋለን ! ብለው ተናገሩ 
  የእናት ሀገር ጥሪውን ተከትሎ ከአራቱም የኢትዮጵያ መአዘናት ለሀገሩ ሉኣላዊነት ቀናኢ የሆነው ህዝብ በገፍ ወደ ታጠቅ ማሰልጠኛ ጣቢያ ተመመ ።
  በመጀመሪያ የከፋ ክ/ሀገር ዘማች ሚሊሻ ቀጥሎ የጎጃም ክ/ሀገር ሚሊሻ እያለ ወደ 300,000 ሺህ የሚጠጋ ህዝባዊ ሰራዊት ለስልጠና ታጠቅ ከተመ ። ታጠቅ አዲስ ማሰልጠኛ ጣቢያ ነበር ።
  300,000 ለሚሆነው ሰልጣኝ የሚበቃና የሚመች መሠረት ልማት አልነበረውም ። ታጠቅ በቂ መጠለያ ፣ በቂ ማብሰያ ፣ በቂ መፀዳጃ ፣ በቂ ጠመንጃና ፣ … አልነበረውም ። ወቅቱም ዝናብ ይጥል ስለነበር የጭቃው ነገርም ለስጠናው ስራ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ነበር ።
  ከሀረር የጦር አካዳሚና ከሆሎታ ገነት ጦር ት/ቤት ስልጠና ላይ የነበሩት እጩ መኮንኖች ትምህርታቸውን አቋርጠው ከሌሎች የጦር ክፍሎች ከተውጣጡ አሠልጣኞች ጋር በመሆን ሰልጣኝ ህዝባዊ ሰራዊቱን ለማሠልጠን ታጠቅ ከተቱ ።
  የእናት ሀገር ጥሪው የተቀበለው የአዲስ አበባና የአከባቢው ህዝብም ዘማች ሚሊሻውን ሊደግፍ ወደ ታጠቅ ተመመ ። የእድር ድንኳኖች ፣ የማብሰያ ድስቶች ፣ የመመገቢያ ሰሀኖች ፣ የመጠጫ ኩባያዎች ፣ …በገፍ ወደ ታጠቅ ተጫኑ ። እናቶች በዓድዋው ዘመቻ የፈፀሙትን ገድል ለካራማራም ደገሙት ።
 በወቅቱ በኢህአፓ የሚደረገውም አፍራሽ ፕሮፓጋንዳና ማስፈራሪያ ሳያስፈራቸው ወደ ታጠቅ አቀኑ ።
በጉዟቸው ላይም
ማን ይፈራል ሞት
ማን ይፈራል
ለእናት ሀገር ሲባል …
በማለት የነሱንም ፣ የዘማቹንም ወኔ ያበረቱት ነበር ።
  በስራቸውም በፈረቃ ለሠልጣኙ እርጥብ ምግብ ያዘጋጃሉ ። ሚሊሻው ወደ ግንባር ይዞት የሚሄደውን ደረቅ ስንቅ ይቋጥራሉ ። ወንዶችም በፊናቸው እንጨት ይፈልጣሉ ፣ ውሃ ይቀዳሉ ፣ የሰልጣኙን ልብስ ያጥባሉ ።
  ኢትዮጵያ የቶሎ ቶሎ ስልጠናውን በተያያዘችው ወቅት ለተከታታይ 10 አመታት ሲሰለጥንና በገፍ ሲታጠቅ የነበረው የዚያድባሬ ሀይል ሐምሌ 3 ፤ 1969 ዓ.ም ላይ በሰፊው የኦጋዴን ክልል ላይ በርቀት ነጥቦች ላይ ተራርቀውና እርስበእርስ ለመረዳዳት በማይችሉበት ሁኔታ የነበሩትን የ3ኛ ክ/ጦር አካል የሆኑትን የኢትዮጵያ የጦር ሰራዊቶችን የተለያዩ ክፍሎችን መግፋት ጀመረ ።
  የኢትዮጵያ ሰራዊት የሚቻለውን መከላከል ቢያደርግም በነበረው ከፍተኛ የኃይል አለመመጣን ምክንያት ሰራዊቱ እየጣለና እየወደቀ ለማፈግፈግ ተገደደ ። ሶማሊያም ገላዲን ፣ ቀብሪደሃር ፣ ደጋሀቡር ፣ ጎዴ ፣ ሙስታሂል ፣ አይሻ/ደወሌ ፣ ገርባሳ ፣ ጭናቅሰን ፣ …የሚገኙ የሠራዊት ክፍሎችን በመግፋት በምስራቅ 700ኪ.ሜ ፤ በደቡብ 300 ኪ.ሜ. ጠልቃ በመግባት የኢትዮጵያን ሉአላዊ ግዛት በኃይል ተቆጣጠረች ።
   ጅጅጋን ተቆጣጥረው የሀረርና ከተማ በመድፍ ቀለበት አስገብተው መደብደብ ተያያዙት ፤ የድሬዳዋም ከተማ አፍንጫ ስር ደረሡ ።
ሶማሊያ በተቆጣጠረችው አከባቢ የሚኖረውን ህዝብ በዚያድባሬ ሃይል የባርነት ቀንበር ስር ወደቀ ። ንብረት ወደ ሞቃዲሾ ተጋዘ ። ሴቶች ተደፈሩ ። በርካታ ሰላማዊ ዜጎችም በግዞት ወደ ተለያዩ የሶማሊያ ከተሞች በገፍ ተጋዙ ።
  በወቅቱ ሶማሊያ እጅግ ዘመናዊውን ስታሊን ኦርጋን (BM ) ጨምሮ አይነተ ብዙ ሩስያ ሰራሽ የጦር መሳሪያ ታጥቅ የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያ በብዛት የታጠቀችው አሜሪካ ሰራሽ መሳሪያ ነው ።
   በጊዜው የኢትዮጵያ ትጥቅ ከሶማሊያ ጋር ሲነፃፀር ኃላቀር የነበረ መሣሪያ ነበር ።
   በወቅቱ  የጂሚ ካርተር ይመራ የነበረው የአሜሪካ አስተዳደር በቀኃሥ ዘመን የተፈፀመውን የተከፈለበት የጦር መሳሪያ ግዢ ውል እንዳይፈፀም በማገዱ ኢትዮጵያ ትልቅ አደጋ ላይ ወድቃ ነበር ።
  ኢትዮጵያም የጦር መሣሪያ ድጋፍ ለማግኘት ወደ ምስራቁ የሶሻሊስት ጎራ ፊቷን አዞረች ። በታህሳስ 1968 ዓ.ም ሶሻሊዝምን በማወጅ አጋርነቷን አሳይቷ ስለነበር ከምስራቁ አለም አመርቂ ድጋፍ ማግኘት ጀመረች ።
  ሶቪየትም ከሶማሊያ ጋር መቃቃር ስለጀመረች ፊቷን ወደ ኢትዮጵያ በማዞር በብዛት የጦር መሣሪያ ድጋፍና የባለሞያ /አማካሪዎች እገዛ አደረገች ።
  እጅግ ፈታኝ ስራ ቢሆንም ኢትዮጵያ ሰራዊቷንም ከአሜሪካ ሰራሽ መሣሪያ ስርአት ወደ ሶቪየት መሣሪያ ስርአት ሽግግር በሚያስደንቅ ፍጥነት አካሄደች ።
  ታጠቅ ጦር ሰፈር ሲሰለጥን የከረመው ህዝባዊ ሰራዊትም በሀገራዊ ወኔና በስልጠና ታግዞ ከኮሪያ የመጣ ሬንጀር ፋቲግ ለብሶ ለሰኔ 18 ለአደባባይ ሰልፍ ትርኢት ተዘጋጀ ።
  በእለቱም የነበረው የሰልፈኛው ሰራዊት እርዝማኔ በአለም ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ በጣም ረጅም ነበር። ጫፉ መስቀል አደባባይ ሆኖ መጨረሻው ከአሮጌው አውሮፕላን ማረፍያ /ጦር ኃይሎች ይደርስ ነበር።
  በወቅቱ ሰልፉን ይታዘቡ የነበሩ የተለያዩ ሀገሮች ታዛቢዎች እና ወታደራዊ አታሼዎች የደማቁን ሰልፍ እና የሰራዊቱን ብዛት በመጠራጠርቸው ከመነሻ እስከ መድረሻው በሂሊኮብተር ተዘዋውረው ከተመለከቱ በኋላ ነበር ያመኑት ።
  በመስቀል አደባባይ የተገኘዉም ህዝብ ለሰራዊቱ ይሰጥ የነበረው ሞራል እጅግ አስደማሚ ነበር።  ህዝባዊ ሰራዊቱም ይህን ዜማ እያዜመ ለሀገሩና ለክብሩ መስዋዕት ለመሆን መዘጋጀቱን በከፍተኛ ወኔ ገለጸ።
ለአንድነቱ
ድሉ እንዲሰምር የነፃነቱ
ወጣ ወረደ : ሄደ ነጎደ ሠራዊቱ ::
አለኝ አደራ
የተቀበልኩት :ከጀግኖች አውራ
እንድትኖር : ሀገሬ ታፍራ ተከብራ
ብሎ ተነሳ : ህዝባዊው ሰራዊት
  ጉዞ ጀመረ
  እየዘመረ
እንዲያበራ
የነፃነት ድል : የአንድነት ጮራ
አውለበለበ የድል በንዲራ
                        እንዲያበራ ::
………….
ሀገሬ
መመኪያ ክብሬ
አትደፈርም ዳር ድንበሬ
ነፃነቴ
ውርሱ የአባቴ
ተደፍሮ ማየት : አልሻም መብቴ
ብሎ ነጎደ : ህዝባዊው ሠራዊት
                                  ጉዞ ጀመረ
                                   እየዘመረ ” …
ህዝባዊ ሰራዊቱም በ9ኝ ክፍለ ጦሮች ተዋቅሮ 8ኛ፣ 9ኛ ፣ 10ኛ እና 11ኛ ክ/ጦሮች እየፈከሩና እየሸለሉ ወደ ምስራቅ ዘመቱ ። 12ኛ ክ/ጦር ወደ ደቡብ ዘመተ ። 14ኛ ፣ 15ኛ ፣ 16ኛ እና 17ኛ ክ/ጦሮችም ወደ ኤርትራና ትግራይ ተላኩ ።
  በአጠቃላይ የኢትዮጵያ አቅምም በፊት ከነበራት 4 ክ/ጦር ታጠቅ የሠለጠነው 9ኝ ክ/ጦር ሲጨመርበት የሰራዊቷ አቅም ወደ 13 ክፍለ ጦሮች አደገ ።
  የሶሻሊስት ኩባ ፕሬዝደንት ጓድ ፊደል ካስትሮም አንጎላ ከነበረው ሰራዊታቸው 18,000 ያህል የእግረኛ ተዋጊና የሜካናይዝድ ኃይል ከህክምና ባለሞያዎች ጋር በጀነራል ኦርላንዶ ኦቾዋ አማካይነት እየተመራ ወደ ኢትዮጵያ ኢንዲንቀሳቀስ አዘዙ ።
  ደቡብ የመንም እስከ 2000 የሚደርስ ጠንካራ የመድፈኛ ብርጌድ ድጋፍ አደረጉ ። ሶቪየት ህብረትም በማርሻል ፔትሮቭ የሚመራ ልዩ ልዩ የአማካሪ ቡድን ላከች ።
  ኢትዮጵያ 300,000 ሚሊሻ በአጭር ጊዜ አሰልጥና ከማስመረቋ በፊት ሶማሊያ ወረራ በካሄደችበት ወቅት ለንፅፅር ይጠቅም ዘንድ የኢትዮጵያና የሶማሊያ አጠቃላይ የጦር አቅም ንፅፅር ይህን ይመስላል ።
                                        ሶማሊያ            ኢትዮጵያ 
ሀ/ እግረኛ ክ/ጦር               8                      4
ለ/ ኮማንዶ ብርጌድ             4                      0
ሐ/ ሜካናይዝድ ክ/ጦር     4                      0
መ/ታንከኛ ብርጌድ              4                      1
ሠ/ BM /ስታሊን ኦርጋን      125                  1
ረ/ ታንክ                                608                  132
ሰ/ ብረት ለበስ ተሽከርካሪ    253                  51
ሸ/ ተዋጊ አውሮፕላኖች          65                    8
  በመቀጠል በከፍተኛ እልህና ቁጭት የተሞላው ህዝባዊ ሰራዊት ከመደበኛ ጦሩ ጋር በመቀላቀል በታጠቀው ሀገራዊ ፍቅርና ወኔ ታግዞ በበርካታ ግንባሮች ተሠልፎ ነባሩን ጦር በማጠናከር የሶማሊያን ተጨማሪ መስፋፋት መግታት ጀመረ።
  በጀግንነት ጥሎ መውደቅ ተያያዘው ። ይህም አልበቃ ብሎት በዘመች ሚሊሻ አማካይነት በነፍስ ወከፍ መሳሪያ እየታገዘ የሶማሊያን ታንኮች በአስደናቂ ጀብድ ይማርክ ገባ።
  በወረራ ከተያዘው ህዝብ ጋርም እየተባበረ የሶማሊያን ወራሪ ማርበድበድ ተያያዘው ። ይህ ሀገርን ከወረራ ለማዳን ርብርብ በሚካሄድበት ወቅትም ከመነሻው የሶማሊያን ወረራ ደግፎ  የቆሙ እንደ ኢህአፓ አይነት ሃይሎች በጦሩ ውስጥ አስርገዉ ባስገቧቸው ኃይሎች ርብርብ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያን ሰራዊት በሚያሳዝንን በሚያሳፍር መልኩ ከኋላ ይወጉት ነበር ።
  በጣት የሚቆጠሩ አውሮፕላኖችን ግን እጅግ የበቁ አብራሪዎቹን የያዘው ጀግና የኢትዮጵያ አየር ኃይልም አለምን ባስደመመ የመዋጋት ብቃቱ በቁጥርና በዘመናዊነት የሚበልጡትን የሶማሊያን ሚጎች በአየር ላየር ውጊያ ከሰማይ ወደ መሬት እንደ ዝናብ ያራግፋቸው ጀመር።
  በአጭር ጊዜ የሶማሊያን ጀቶች ከኢትዮጵያ የአየር ክልል ካፀዳ በኋላ የሶማሊያ ግዛት ዘልቆ በመግባት የነዳጅ ዲፖዎችን ፣ የስንቅና ትጥቅ መጋዘኖችን ፣ የአውሮፕላን መንደርደሪያ ሜዳዎችን ማውደም ተያያዘው ።
  አከታትሎም በሰፊው አውደ ግንባር የተጠመዱትን እሳት የሚተፋትን የጠላትን ስታሊን ኦርጋኖችን ላንቃቸው ዘጋቸው ። የእደላ መስመሮችን ቆረጣቸው።
  የአየር ኃይሉ ጀግኖች አብራሪዎቹ ያለምንም እረፍት በመብረር በአጠቃላይ የወራሪውን ኃይል አናት አናትን እየቀጠቀጡ አዳከሙት ።
የአየር ኃይሉን ሽፋን እየተጠቀመም ህዝባዊ ሰራዊቱ ከህዳር አጋማሽ 1970 ዓ.ም ጀምሮ ከመከላከል ደረጃ ወደ ሰፊ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ ተሸጋገረ ።
   መሪር መስዋእትነት እየከፈለ የሶማሊያን እግረኛና ሜካናይዝድ ጦርን አከርካሪ መስበሩን ቀጠለበት ። በጠላት ከበባ ወድቀው የነበሩት ድሬዳዋን እና ሀረር ከተሞችን ከጠላት መንጋጋ አስጥሎ ለቀጣዩ ወሳኝ ፍልሚያ ተዘጋጀ
የካቲት 23 /1970 ዓ.ም የዓድዋ ድል እለት የትዮጵያ ጦር  በጭናቅሰን እና በቆሬ በኩል ወደ ጅጅጋ አቅጣጫ የተጠናከረ ቅንጅታዊ የጎህ መጥቃት ዘመቻ ከፈተ ። የሶማሊያ ጦርም ጥቃት ይመጣብኛል ብሎ ብሎ ካልጠበቀው አቅጣጫ በመወጋቱ ተደናገጠ ። ጅጅጋንም ላለመልቀቅ ተሟሟተ ። ሶማሊያ በዚህ መደናገጥ ውስጥ እያለች ከጀልዴሳ ግንባር ሌላ ጥቃት ተከፈተባት ። የሶማሊያም ሰራዊት ጅጅጋን ከለቀቀ ትልቅ የሞራል ውድቀት እንደሚገጥመው ያውቃል ። በመሆኑም ከጅጅጋ በስተምእራብ በኩል ባለው ካራማራ ተራራ ላይ ማዘዣ ጣቢያውን በመስራት በከፍተኛ ደረጃ ተከላከለ ። ሆኖም በለስ አልቀናውም ።
ጥቃቱ በሁሉም ግንባር የተከፈተ በመሆኑ አጋዥ ሰራዊት ከየትም ማንቀሳቀስ አልቻለም ። በውጤቱም የካቲት 26 ረፋድ ላይ በካራማራ ከባድ ሽንፈት ተጎነጨ ። በውጤቱም ከሞትና መቁሰል የተረፈው የጠላት ሠራዊት መሳሪያውን እያንጠባጠበ ጅጅጋን በመልቀቅ ወደ ሀርጌሳ መስመር ፈረጠጠ ።
እሁድ የካቲት 26/1970 ዓ/ም ላይ በአከባቢው የነበረ ሰራዊት ወድቃና ተዋርዳ የነበረችውን  ሰንደቃችንን መልሶ ከፍ አድርጎ በክብር ሰቀለ ። የዛሬ 42 አመት እንዳይድን እንዳይሽር ተደርጎ የተሰበረው የዚያድባሬ ተስፋፊ ኃይል በቀጣይ ቀናቶች ጦርነቱን በይፋ አቁሞ በወረራ ተቆጣጥሯቸው ከነበረው ከቀሪ የኢትዮጵያ ሉኣላዊ መሬቶች ተጠቃሎ ወጣ ። ይህ ድል እውን እንዲሆን ግን የበርካታ ውድ ኢትዮጵያዊያን የደምና የአጥንት መስዋእትነት አስፈልጎ ነበር ። ከኢትዮጵያዊያን በተጨማሪም የወንድም ህዝብ ልጆች የሆኑት የኩባዊያንና የደቡብ የመናዊያን ውድ የህይወት መስዋእትነት ተከፍሎበታል ።
የደረሰው ጉዳት በአጭሩ ይህን ይመስላል ።
ሠራዊት       የሞተ           የቆሠለ          የተማረከ
ኢትዮጵያ         18,000        29,000         450
ኩባ                  163                                   1
የመን                100
ሶማሊያ         15,900       26,200         1,785
  የካራማራ ድል ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ሉአላዊነት ያላቸውን ቀናኢነት ቀፎ እንደተነካ ንብ በህብረት በመቆም ገልፀውታል ። ለሠንደቃቸው ያላቸውን ልባዊ ፍቅር ውድ መስዋዕትነት በመክፈል በደማቅ የደም ቀለም ፅፈውታል ። ለዘመናት የተገመደው የማይበጠስ አንድነታቸውን በደም ፍሳሻቸውና በአጥንት ፍላጫቸው በድጋሚ በፅኑ መሠረት ላይ ገንብተውበታል ።
   ከታላቁ የዓድዋ ድል ቀጥሎ የኢትዮጵያዊያን ህብረትና አንድነት ማሳያ የሆነው የካራማራ ጦርነት ለማመን የሚቸግሩ በጀብድ የተሞሉ ጀግንነቶች በተናጠልና በቡድን ተከናውነውበታል። ተዘርዝረው ከማያልቁ የሠራዊቱ ጀብዶች መካከል ለምሳሌ ያህል ሁለቱን ልጥቀስ ።
  የሀረር አካዳሚና የበረራ ት/ቤት ጥምር ምሩቅ የሆኑት የአዲስ አበባው ፍሬ  የአየር ኃይሉ ነብር ጀግናው ብ/ጀ ለገሰ ተፈራ በF5-E ጀታቸው አማካይነት በአየር ላየር ላይ ውጊያ አምስት የሶማሊያ ሚግ 21 ጀቶችን በመምታት ከአየር ወደ መሬት አራግፏቸዋል።
  በርካታ ጀብድ ፈጽመው የድሉ መጨረሻ ሰአት ላይ በፊልቱ ግንባር ላይ አውሮፕላናቸው ተመትቶ በጠላት ተይዘው ለ11 አመታት በሶማሊያ እስር ቤቶች የስቃይ ህይወት አሳልፈው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
  ለወደር የለሽ የጀግንነት ስራቸውም በጊዜው የሀገሪቱ የመጨረሻ ደረጃ የሆነውን የህብረተሠባዊት ኢትዮጵያ ወደር የለሽ የጀግና ሜዳይ ተሸልመዋል ።
  ሌላው ጀግና ደግሞ የእናት ሀገር ጥሪ ሰምቶ በለጋ እድሜው ከቀድሞ ወለጋ ክ/ሀገር አሶሳ አውራጃ ቤጊ ወረዳ የመጣው ሻለቃ ባሻ አሊ በርኬ ነው።
  ጀግናው አሊ በአቡሸሪፍ ግንባር  ሶስት የጠላት ታንኮችን በእጅ ቦንብ በማቃጠል በግንባሩ ለነበረው ድል ወሳኝ ሚና ተጫውቷል ። ለዚህም ስራው የላቀ የጀብድ ሜዳይ ተሸላሚ ሆኗል ።
  ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከአራቱም የሀገራችን ማዕዘናት የብሔርና የሀይማኖት አጥር ሳያግዱት በጠነከረ የአንድነት መንፈስ በመላበስ ደሙን አፍስሶ ፣ አጥንቱን ከስክሶ ነው ይህንን ታላቅ ድል ማስመዝገብ የተቻለው።
   ይህ ድል ዕውን እንዲሆን ከኢትዮጵያዊያን በተጨማሪም የወንድም ህዝብ ልጆች የሆኑት የኩባዊያን የሩሲያውያንና የደቡብ የመን ውድ ዜጎች የህይወት መስዋእትነት ተከፍሎበታል።
   ዘንድሮ 42 ዓመት የሚሞላውን የካራማራ ድል የመታሠቢያ በዓል ነገ ሐሙስ የካቲት 26 ቀን 2012 ዓ.ም ጥቁር አንበሳ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት የመታሠቢያ ፓርክ (ትግላችን ሐውልት) ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ ሀገር ወዳድ እና ታሪክን ዘካሪ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዕለቱ በቦታው በመገኘት የድሉን በዓል ላይ እንድትታደሙ ከወዲሁ እንጋብዛለን።
   መንግስት በቀጣይ ይህንን ኢትዮጵያዊያን በአንድነት መንፈስ በህይወትና በአካል መስዋዕትነት የከፈሉበትን ታላቅ ሀገራዊ የህዝብ ድል ትኩረት ሰጥቶት በቀጣይ ጊዜያት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍ ብሎ እንዲከበር እና ትውልዱ አባቶቹ ከሰሩት ከዚህ የጋራ የድል ታሪክ ተምሮ አንድነቱን እንዲያጠነክር አበክሮ እንዲሰራ ጥሪ እናስተላልፋለን።
ተፈፀመ!!!!
ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ ለጀግኖቹ የካራማራ ሠማእታት ይሁን  !!!
ኢትዮጵያ ምንግዜም በክብር ትኑር !!!
Filed in: Amharic

Thursday, May 18, 2023

History 101: Fiction and Facts on Oromos of Ethiopia Prof. Feqadu Lamessa

Oromia region since 1987
 


History 101: Fiction and Facts on Oromos
of Ethiopia

Prof. Feqadu Lamessa

(a guide for foreign journalists on Oromos and Ethiopian history)

(ADAMA, Ethiopia) - Recently, the Qatar-based media al Jazeera has published several articles concerning the Oromo people of Ethiopia. (http://www.aljazeera.com/indepth/opinion/2013/07/2013714133949329934.html) It is the first international media outlet to extensively report on our people and it should be praised for bringing our cause to the world stage.

One of the benefits of this exposure is it forces Ethiopian authorities to address human rights abuses in the country and to let them know that the world is watching. Oromos and other Ethiopians have been struggling for equal rights and democracy for decades. While it is important to report about Oromo people' background and historical perspectives, it is however vital that we report accurate information. Instead of benefiting us, reporting inaccurate or biased information can actually harm our struggle for democracy. Instead of creating national consensus and peace, it can instigate bitterness and anger.

One of the reasons al Jazeera reported inaccurate information about Oromo history is because it depended on one-sided sources, especially from members or supporters of Oromo groups outside of Ethiopia (diaspora OLF, OFDM etc). But nobody can blame al Jazeera media because most people inside Ethiopia would be too scared to speak or contribute. The only option al Jazeera or any foreign media has is to use diaspora/refugee/external sources outside Ethiopia. This is a dilemma all foreign media outlets face while reporting about third-world countries like Ethiopia.

For educational purposes, some corrections are provided below to fix inaccuracies reported on al Jazeera media regarding Oromo history and our struggle for democracy. The corrections below are supported by non-political scholars, but they might be rejected by biased politicians (both from ruling party and from opposition party) for the obvious reasons. However, they are based on historical textbooks, European authors and scholarly accounts.

Fiction #1:"Between 1868 and 1900, half of all Oromo were killed, around 5 million people"Fact #1: This is one of the most repeated inaccuracies, usually told by Secessionist Oromos, radical ethno-nationalist politicians outside the country or pro-OLF history revisionist websites like gadaa.com et al. However, the undisputed fact is that even the total Ethiopian population (the sum of dozens of ethnic groups) was much less than 5 million in the late 1800s, let alone one ethnic group being 10 million. So claiming that 5 million ethnic Oromos were killed by Emperor Menelik's forces does not add up. The truth is several thousand Oromos were in fact killed during battles of that era. It was not a "genocide" as some politicians claim but it was a massacre of the ill equipped southern forces defeated by the Shewan military of Emperor Menelik which had more European weapons. Throughout those decades, the truth is more Oromos were killed by other Oromos than by non-Oromos because competing Oromo Clans often traded for weapons to have an upper hand against their local competitors, who were often their fellow Oromo and Sidama neighbors.  And it was not the first lop sided victory of that era in Africa because various communities from all corners of Ethiopia had attacked one another during the "resource battles" and whichever group had more modern weapons had the upper hand. To summarize, Professor Mengistu Paulos of Jimma University said it best when describing right-wing Oromo liberation philosophy:-- "Most fictional accounts of 'Oromo history' blindly accepted as facts by some misled people are manufactured by former politicians turned Pseudo-historians  like OLF writer Asafa  Jalata, who is renowned for abuse of paraphrasing, often with out-of-context citations. For example, while quoting the 19th century Russian Alexander Bulatovich (who provided an 'educated guess' of annihilation of almost half Ethiopian population by disease, famine and war, including internal conflict between Oromo clans and with Abyssinians), the OLF-writer Asafa Jalata infamously claimed half Oromo population was killed by 'evil' Amharas.  This was purposely done by Mr. Jalata to create a foundation for ethnic hatred between Oromos and Amharas. Ironically, even Mr. Bulatovich himself never had the capacity nor the legitimacy to do a reliable census, as he spent just a couple of months walking around Oromia and hunting elephants in 1890s."Fiction #2:"…. largely Muslim Oromo people"Fact #2:This is a phrase seen in some media outlets but not most. Oromo people have never been a predominantly muslim people. In fact, both Christianity and Islam is not our ancestral religion because we have practiced an indigenous traditional religion for centuries before. Gradually, Islam and Christianity were both adopted (during Oromo migrations) by us and imposed (during conquest of our lands by Abyssinian/Christians & Somalis/Islam)  on us thru out history. Even today, both the two major religions have equal representation among Oromos. The latest official 2007 census showed that around 48% of Oromos practice Christianity (Both Orthodox & Protestant) while around 47% of Oromos practice Islam. Yet, word on the ground is that the Islam population might soon surpass Christianity among Oromos in the future because Orthodox Christianity is decreasing inside Oromia. Fiction #3"Abyssinians labelled Oromos the derogatory word 'Galla'"Fact #3:For many decades, this false statement has been used by Oromo separatists to create emotional resentment among Oromos against Semitic Abyssinians (Amharas, Tigrayans and Gurages).  The fact is the derogatory word "Galla" was first used by Arab and muslim Somalis to describe Oromos as "gal" meaning "outsiders" and "Pagans." Muslims used this label during Oromo migration because Oromo people had their own religion which the Muslims believed was paganism. Nonetheless, this derogatory word was gradually adopted and used by other Ethiopians. Fiction #4:"Oromos were colonized by Emperor Menelik"Fact: #4Another popular claim made by secessionist Oromo politicians (and usually repeated by foreign journalists) is the fiction that Oromo people (as a whole ethnic group) were colonized by another ethnic group. Usually, the slogan goes "Abyssinians colonized Oromos" etc. This claim is popular among the Oromo Liberation Front (OLF) organization and consequently among some Diaspora Oromo nationalists living in America and Europe.  While a different version or a re-arrangement of the wording might still be true…in general, the Oromo nation as a whole was never colonized by another Ethiopian ethnic group. To start with, even a united one Oromo nation did not exist at those times. All non-political historical textbooks show the existence of battles between multi-ethnic BUT monolingual communities for many centuries through out Ethiopia. Even in northern Ethiopia (traditional "Abyssinia") Oromos have migrated and mixed so much with Tigrayans, Amharas, Afars etc for centuries that the "Abyssinia" state itself was never a one-ethnic state. In fact, even around the 1700s, Rayya Oromos and Yejju Wallo Oromos conquered and dominated a portion of Amharas and Tigrayans; and thus made Afan Oromo the official language of Abyssinia for that brief period. Meaning: clans and ethnic groups have mixed up in Ethiopia for over a millennium but the dominant ethnic group always imposed its language since it was convenient. This linguistic domination however was not always as exploitive and as vilified as it is today; because many of the ethnic groups living along trade centers and trade routes often spoke the languages of other ethnic groups already, because there was financial or commercial incentive to do so. This is the background of the region. Therefore, when it comes to the Emperor Menelik era, all historians have argued that it is more factual to say a predominantly Amharic language speaking community gradually conquered a predominantly Afan Oromo language speaking community in the 1800s. So this does not mean an Oromo ethnic group was conquered by an Amhara ethnic group. In fact, just like Amharas of the north were divided,Oromos were also divided and in conflict among themselves. The obvious evidence for this comes from the fact that the Amhara Emperor Menelik was imprisoned by other Amhara regional kings when he was younger. And when he was freed, Oromo clans were also in fierce battles amongst each other, so much so that the Tullama Oromo, Limmu and Macha Oromos created an alliance with the Shewan Amharas of Menelik, leading to the infamous battles of 1880s that led to this said alliance easily crushing the non-allied Oromos in various bloody wars. In short, Oromos as a one whole were never colonized by exclusively non-Oromos. In fact, the original founders of the OLF organization themselves never believed it so they did not emphasize the word "colonization" in the beginning. But in the mid-1970s, OLF leaders needed to mobilize Oromos against Emperor Haile Selassie (who was half Oromo himself) and to justify the call for "Oromia independence" from "colonial Ethiopia." Therefore OLF had to create a bad cop-good cop scenario for their convenience and simplified history for their people to create national resentment. This helped OLF to portray Oromos as suddenly being colonized by this foreign ethnic group (Amhara) that we (Oromos) have never came in contact with before.  This is common tactic used by national liberation movements around the world. The truth that most Ethiopians know is that Shewa based Oromos and Amharas (ethnically mixed Ethiopians) were the main creators of modern Ethiopia. In his book "Who are the Shoans," the historian and anthropologist, Dr. Gerry Salole once summarized that: "In terms of descent, the group that became politically dominant in Shewa (and subsequently in Ethiopia) was a mixture of Amhara and Oromo."   In Conclusion, the above are 4 of the main issues that create confusion for foreign journalists who report on Oromo people and Oromo politics in Ethiopia.  While it is vital that al Jazeera and other media outlets cover the current suffering of Oromos and other Ethiopians, it is necessary to report responsibly. Otherwise, creating confusion and resentment between the younger Ethiopian population causes more problems than solutions. In reality, not just Oromos, but all Ethiopians have suffered under several governments and the only way they can achieve freedom and lasting democracy is when united, not when divided by tribes or not when being polarized by historical lies presented as truth.  It is important that foreign media outlets make corrections or report accurate information to avoid inflammatory statements that are destructive and counter productive against Oromos and all Ethiopian people' ongoing struggle for democracy, development and justice.Feqadu Lamessa is a former Adama University professor and writer 

Friday, April 28, 2023

በ‹‹ሰባራ ወንበር›› እና በ‹‹የፉክክር ቤት›› መካከል ላይ.. .!!! (በድሉዋቅጅራ)

 




ከአመት በፊት ‹‹ዴስትኒይ ኢትዮጵያ›› የተባለ ድርጅት የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና ታዋቂ ግለሰቦችን ሰብስቦ፣ ሀገራችን በወቅቱ የምትገኝበትን ሁኔታ መሰረት አድርጎ የወደፊት እጣ ፋንታዋን የሚያመላክት ውይይት አድርጎ ነበር፡፡ በውይይቱ መጨረሻ የተደረሰባቸው ሴናሪዎዎች አራት ናቸው፤

.

1. ‹‹ሰባራ ወንበር›› (ለመልካም አስተዳደር ፍላጎት ያለው ግን ተግባራዊ ያልሆነ መንግስት) 

2. ‹‹አጼ በጉልበቱ›› (አንባገነን መንግስት)

3. ‹‹የፉክክር ቤት›› (ክልሎች ተጠናክረው እርስ በርስ የሚፈታተሹበትና የፌደራል መንግስቱ  የደከመበት)

4. ‹‹ንጋት›› (በትክክለኛው መንገድ ላይ የምትገኝ ወደ ዲሞክራሲ የምትጓዝ ሀገር)፡፡

.

በስብሰባው የተሳተፉት የፖለቲካ መሪዎች ሀገራችንን ወደ ‹‹ንጋት›› ለማድረስ ተስማምተው (አጨብጭበው) ተለያዩ፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘው የተስማሙበትን ለህዝባቸው በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት አሳዩ፡፡  . . . ዛሬ ከአንድ አመት በኋላ ሀገራችን ‹‹ሰባራ ወንበር›› እና ‹‹የፉክክር ቤት›› መካከል ትገኛለች፡፡ አብዛኞቹ የፖለቲካ መሪዎች እንኳን መስማማታቸውን መወያየታቸውን ረስተውታል፡፡

.

አንዳንዶች ‹‹ወደ ፈላጭ ቆራጭ የአምባገነንነት ስርአት እየሄድን ነው›› ይላሉ፤ አይደለም፡፡  የአምባገነንነት ዋናው መገለጫ፣ የመንግስት እኔ ያልኩት ብቻ ይሁን ማለት፣ ዜጎችን አስሮም ይሁን ገድሎ የተናገረውን (ፍላጎቱን) ለመተግበር ያለው ቁርጠኝነት፣ በስልጣኑ ከመጡበት የትኛውንም ሰብአዊ መብት ከዜጎች ላይ ለመግፈፍ ወደኋላ አለማለቱ፣ . .  የመሳሰሉት ናቸው፡፡ አንባገነን መንግስታት ጠንካራ ሰራዊትና የስለላ ድርጅቶች አሏቸው፡፡ ጽዋው ሞልቶ ህዝብ እስኪገነፍል ድረስ ያለ እነሱ ታጣቂ፣ ያለ እነሱ ገዳይ አይኖርም፤ ኮሽ አይልም፡፡

.

አሁን ያለው መንግስት ከላይ የተጠቀሱትን አያሟላም፡፡ ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ታጣቂዎችና ገዳዮች የሌሉበት የሀገሪቱ ክፍል የለም ማለት ይቻላል፡፡ የተናገረውን የማስፈጸም አቅሙ ዜሮ የሚባል ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በፌደራልና በክልል ያሉ ባለስልጣናትና ፖሊሶች ግጭትና ግድያን ሪፖርት ከማድረግ ዘለው፣ ሊቆጣጠሩት አልቻሉም፡፡ ይህ ከመለመዱ የተነሳ ባለስልጣናቱና የጸጥታ አስከባሪው ህግን ማስከበርን የማይመለከታቸው ጉዳይ አድርገው ቆጥረውታል፡፡ ህጻናትና እናቶች በግፍ በተገደሉበት ቀን ጠዋት ተነስተው ስራ ይገባሉ፤ ስብሰባ ይሰበሰባሉ፤ የመሰረት ድንጋይ ያኖራሉ፤ የምረቃ ሪቫን ይቆርጣሉ፡፡ . . . ይህ ዋናው ‹‹የሰባራ ወንበር›› ሴናሪዎ ባህርይ ነው፤ የማስፈጸም አቅም ማጣት (ይህ ደግሞ ካለመቻል ወይም ካለመፈለግ ሊመነጭ ይችላል)፡፡

.

መንግስት አንድን ህገወጥ ተግባር መቆጣጠር ባልቻለ ቁጥር የህግ አፍራሾቹ ጉልበት እየጠነከረ ይሄዳል፡፡ በአንጻሩ መንግስት እየደከመ፣ እየደከመ እንደማያስቀምጥ ሰባራ ወንበር ይሆናል፡፡ አንድ ቀን ጉልበቱ ዝሎ ልቀመጥ ሲል ነው ወንበሩ እንደተሰበረ የሚያውቀው፤ይዞት ሲወድቅ፡፡ ዛሬ ወደዚያ እየገሰገስን ነው፡፡

.

የፌደራል መንግስት የማስፈጸም አቅም ማነስ የክልሎችን አቅም ያጎለብታል፤ የፌደራሉን መንግስት ስራ እየሸራረፉ መውሰድ ይጀምራሉ፡፡ ይህ ደግሞ ወደ ‹‹የፉክክር ቤት›› ሴናሪዮ የሚወስድ መንገድ ነው፡፡ ዛሬ ክልሎች በአስተዳደር ወሰናቸው ከሚፈጸመው ግድያና ግፍ በላይ በተጎጂ ክልሎች ጥቃቱ እንዲቆም የሚቀርበው ጥያቄ የቃላት አመራረጥና አቀራረብ ያስቆጣቸዋል፡፡ የፌደራሉ መንግስት በየክልሉ የሚፈጸሙትን ግድያዎችና ህገወጥ ተግባራት ሙሉ በሙሉ ማስቆም ባለመቻሉ፣ ክልሎች ጡንቻቸውን አጠንክረው እራሳቸውን ለመከላከል እየተጣደፉ ነው፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ‹‹የፉክክር ቤት›› ሴናሪዮ ዋና መገለጫ፡፡ . . .  በነገራችን ላይ እነዚህ ሁለት ሴናሪዮዋች ከአንባገነንነት በላይ ሀገር አፍራሾች ናቸው፡፡ መሪን በማስወገድ አንባገነንነትን መታደግ ይቻላል፡፡ ሁለቱ ግን ጦሳቸው ሀገርን እስከማፍረስ ይደርሳል፡፡

.

እንግዲህ ዛሬ ምርጫ የምንመዘገበው በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆነን ነው፡፡ በዚህ ሰላም ጠፍቶ፣ ግድያና መፈናቀል አዘቦታዊ በሆነበት ሁኔታ ውስጥ ሆነን ውጤቱ በተወዳዳሪ ፓርቲዎች ሁሉ ተቀባይነት ያለው ሰላማዊ ምርጫ የማድረግ እድላችን ጠባብ ነው፡፡ ከምርጫው ወደ ‹‹ንጋት›› ሊያራምድ የሚችል ፋይዳ ያለው ነገር እናገኝ ዘንድ፣ የፌደራሉ መንግስት ከክልል አመራሮች ጋር በወጥነት ተቀናጅቶ ግድያን ማስቆምንና ህግን ማስከበርን ተቀዳሚ ተግባሩ ማድረግ አለበት፡፡