ወያኔ/ህወሓት የዱላ ቅብብል ሩጫው ላይ ተግቶል፡፡ ወርቁን ለማግኘት የቡድን ስራውን ተግቶ እየሰራ ነው፡፡ መለስ ዜናዊ የጥቅለላውን ዱላ አሁን አለሁ አለሁ ለሚለው ቡድን አስረክበው ከመሮጫ ትራኩ ወጥተዋል፡፡ ዱላ ሰቅለዋል፡፡ የትግራዩ ቡድን በኤርትራም በጎንደርም ልምምዳቸውን ያደርጉ የነበሩ ሮጮችን ምንም አይነት የዱላ ቅብብል ሩጫ ውድድር ፊሽካ ሳይነፋ ለልምምድ በተሰጠውና በያዘው ዱላ እየሰነዘረ፤ እየፈነከተ ሮጮችን ከልምምድ ብሎም ከውድድር ውጭ እያስወጣ ከዚህ ደርሶል፡፡ የዱላ ቅብብል ሩጫ ቡድኑ በጥብቅ ማዕከላዊነት ስለሚመራ ዱላውን የያዘ ሮጭ ሸምጥጥ ከተባለ ይሸመጥጣል ፤ ምናልባትም ተቀናቃኝ ሮጭ ከተገኘ በቻለው አቅም እርምጃ እንዲወስድ መመሪያ ይሰጠዋል፡፡ የዱላ ቅብብል ሩጫው ቡድን የመሠረተው ከሌላ ቡድን ከድቶ ከመጣ በኀላ ነው፡፡ ወያኔ/ህወሓት ሻብያ ከተባለው ቡድን ጋር በአንድ ቡድንም በመታቀፋም በተናጠልም ተወዳድረዋል፡፡ ነገር ግን ውድድሩ ደርቢ ሲሆንበት ነው የተነጠለው ፡፡ ባስበው ባስበው ደከመኝ እንዳለው ገበሬው ፤ ደርቢው ይቅርብኝና ብቻየን ነው የምሮጠው ፤ የምን አሮሮጭ ነው ብሎ ዱላው ተቀብሎ ተቀየሰ፡፡ አሁን ይኸን ዱላው ይዞ አስሩጦቸው የሚሮጡለት ደርቢ ሳይሆኑ መደበሪያ የሆኑ የቡድን አባለት ሲያፈላልግ ነው ይኸ ጉደኛ ቡድን ያደራጀው፡፡ የዱላ ቅብብል ሩጫው ተጀምሮል፤ ወያኔ/ህወሓት ዱላውን ይዞ እየተንሳቀሰ ነው ፤ብዙም አይሮጥም ዋናው እቅዱ ማሮሮጥ ይመስላል፡፡ ሩጥ ስትለው የሚሮጥ ተኛ ስትለው የሚተኛ እያለ፡፡ አቀበለው፤ ለብአዴን ሰጠው ፤ብአዴን አቤት ሩጫ ሲችል ፤ እንዲያውም በመጨረሻ እንደተገመገመው ለቡድኑ ወርቅ ማግኘት ከፍተኛ አስተዋፆ አርጎል፡፡ ብአዴን ለኦህዴድ አቀበለ፡፡ኦህዴድ ተቀብሎ ሽምጥ እየጋለበ ነው፡፡ ከመሮጫ ትራኩ ላይ የተገኙትን ተወዳዳሪዎች አንዴ በግል መወዳደር አይቻልም እያለ እያወናበደ ሌላ ጊዜ በያዘው ዱላ እየቀጠቀጠ ያስወጣል፡፡ የዱላ ቅብብሉ ሩጫ ከኦህዴድ ወደ ሶዴፓ ሲሄድ ፍሰቱን አሌጠበቀም፡፡ በዚህ መዘናጋት ኦህዴድ በያዘው በያዘው ዱለ አንድ ጊዜ ሶዴፓን ነርቶ ዱላውን ያቀብለዋል ፡፡ ሮጩ ሶዴፓም የዱላ ቅብብሉ ስለገባው ዱላውን ተቀብሎ አፈተለከ እግረመንገዱን በያዘው ዱላ ሞራል አልሰጡኝም የሚለውን ያገኘውን ተመልካች እየጨረገደ ይሄዳል፡፡ የዱላ ቅብብሉ ሩጫ በህገ-አራዊት ስለሚመራ እንሮጣለን ብለው ሩጫ የጀመሩ የሌሎች ቡድን ሮጮች ዱላቸው አስረክበው ከውድድር ትራኩ ወጥተዋል፡፡ ሶዴፓ ዱላውን ይዟ የመጨረሻ ዙሩን አክርሮ እየሮጠ የወርቅ ዋንጫውን ለማንሳት ቆምጦል፡፡ የዱላ ቅብብል ህጉ በህገ-አራዊት የሚመራ በመሆኑ ሁሉም የዱላ ቅብብል ሩጫ የቡድኑ አባላት እኩል ናቸው ነገር ግን አንዳንዶቹ ደግሞ የበለጠ እኩል ናቸው የሚል ህግ ስላለው የወርቅ ዋንጫው በክቡር ትሪቡኑ ቀርቦ የተቀበለው እና ከፍ አርጎ ወደ ደጋፊዎችና ተመልካች እየደነፋ ያነሳው ወያኔ/ህወሓት የተባለው ዱለኛ ሮጭ ነው፡፡ ከክቡር ትሪቡኑ ላይ ሆኖ ዋንጫውን ከፍ ሲያደርግ በስታዲየሙ የተሰበሰበው ህዝብ በአንድ ድምፅ ነጎድጎዳማ የማጉረምረም ድምፅ ሲያወጣ ዋንጫውን የያዘው ዱለኛ ሮጭ የጨው ሰማዕታት ሀውልት ሆኖ ቀረ፡፡ ይኸው ከዚያ ወዲህ የሰማዕታት ሀውልት እናቆማለን፡፡
አብራሃም ለቤዛ
Followers
Thursday, September 7, 2017
ሁሉም መብቶች ለሁሉም!!!
ሁሉም መብቶች ለሁሉም!!!
----------------//---------------
ዘር ፤ቀለም ፤ሃይማኖት በሰብዓዊነትን ተተክቶ
ሕይወት ክቡር ሁና ደህንነቶ ፀንቶ
ብዝበዛ፤ ጭቆና ፤ ሽኩቻ ከአገር ተወግዶ
አገር ሰላም ሁና ፍትህ እኩልነት ሁሉን ተዋህዶ
በእምየ ኢትዮጵያ መቼ ነው የማየው?
ዴሞክራሲ ሰፍኖ ህግ የበላይ ሁኖ
በሰላማዊ ትግል ስልጣን ከህዝብ መጥቶ
ገደብ ተቀምጦ ተጠያቂነት ጎልቶ
ፍርድ ነፃ ሁኖ ጣልቃ ገብነት ቀርቶ
በእምየ ኢትዮጵያ መቼ ነው የማየው?
ሃይማኖት ፤ ባህል፤ቋንቋ ሆነው ጌጦቻችን
አንዱ አንዱን ሳይኮንን ሳይሆኑ ሳንካችን
ሰብዓዊነትን ሰብከው እውቀትን አስፋፍተው
ፍቅርን አጎልብተው ሰላምን አፍርተው
በእምየ ኢትዮጵያ መቼ ነው የማየው?
ዛሬ ሌላው ዓለም ተራቆ ዲሞክራሲ ጎልብቶ
ሰላም ደህንነቱን ለህግ አደራ ሰጥቶ
ህግ የበላይ ሁኖ ፍትህ አስገኝቶ
ሰርተው ይኖራሉ አደራቸው ወጥቶ
በኢትዮጵያ ምድር በአፍሪካችን አህጉር
የዴሞክራሲ እጦት የፍትህ ባይተዎርነት
ልማትም ህልም ሁኖል ደህነትም ቅዠት
ረሃብ፤በሽታ፤ ድንቁርና፤ ጦርነት ሆነውናል ሕይወት
ይህ ሁል ተወግዶ ሰብዓዊነት ለምልሞ
በእምየ አፍሪካ መቼ ነው የማየው?
አብራሃም ለቤዛ ህዳር 21/ 19 99 ዓ/ም
Wednesday, August 30, 2017
እንቦጭ ና ወያኔን ነቅለን የጣልን ለት!
እንቦጭን ከጣና ወያኔን ከአፍር
ላይ ነቅለን የጣልን ለት፤
የባህርዳር ፈርጥሽ የአፋር ገሞራ አለት፤
ታትሞ ይቀራል በአለም-አቀፍ
መዝገብ ይሆናል ቅርስ ውበት፤
መቼ ይጎልና አሳውም ከጣና በከል
ወተቱ አፋር ቤት፤
ሕብረታችን ይታይ አንዱ ለአንዱ ይድረስ ፤
ዋጋ ያስከፍላል መታገስ እኛ
ዘንድ አስቲደርስ ፡፡
የማህበራዊ ልማት ልማት አጥኝዎች
ጥናቶቻቸውን ተደራሽነት ለመጨመር የገጠሩን ማህበረሰብ አሳታፊ የሆነ የጥናት መንገድ (Participatory Rural
Appraisal) መጠቀምን ይመክራሉ፡፡ እነዚህ የጥናት መንገዶች ተግባራዊ ማደረግ ለጥናታችን ግብዓት የሚሆነን መረጃ ማንበብና
መጻፍ ከማይችለው (However, literacy and numeracy are quite different) የማህበረሰብ ክፍል ለጥናታችን
ግብዐት የሚሆነንን መረጃ በአግባቡ ለማግኘት ያግዘናል፡፡ ለጥናታችን ግብዓት መረጃ ማግኘታችን ለጥናታችን የመፍትሄ አቅጣጫ ለማመላከት
የራሱ ጉልህ አስተዎጽኦ አለው፡፡
የገጠሩን ማህበረሰብ አሳታፊ
የሆነ የጥናት መንገድ (Participatory Rural Appraisal) ውስጥ ለወሳኝ ክስተቶች መረጃ ማግኛ ዘዴ (Timeline/Historical
Mapping) አንዱ ሲሆን የማህበራዊ ልማት ልማት አጥኝዎች በጥናታቸው አካባቢ ወደ ሆላ ተጉዘው ምን ምን ክስተቶች እንደነበሩ
የጥናቱ ተሳታፊዎችን የሚጠይቁበት መንገድ ነው፡፡
ከላየ ያለውን ሃተታ ያነሳሁት
በአፋር ክልል ላይ ስለተከሰተው “PROSOPIS” የተባለ አረም
የማህበራዊ ልማት አጥኝዎች የተቸገሩበትን ጉዳይ ስላየሁ ነው፡፡ ይህ
ዓረም ወያኔ እየተባለ በአፋር ነዎሪዎች ዘንድ የሚታወቅ ቢሆንም
አንዳንድ የማህበራዊ ልማት አጥኝዎች የጥናት ወረቀቶች ስመለከት ደርጊ
እያሉ በጥናታዊ ፅሁፋቸው ገልጠውታል፡፡ በአፋር የሚገኘው ወያኔ የተባለው አረም ከወያኔ ጋር አብሮ መጣ ብለው ስለሚያምኑ
እና ለ26 ዓመት በአፋር የሚገኝ ሆኖ በአርብቶ አደሩ የግጦሽ መሬት ላይ ወረራ በማካሄድ ለአርብቶ አደሩ የራስ ምታት ሆኖበታል፡፡
እንቦጭ በጣና ስንት ዓመት ሆኖት ይሆን?
ብዙ ብር ወጥቶባቸው ጥናት የምታደርጉ
ተቋማት ወደ እውነታው ተመለሱ፡፡ ጥናት ማድረግ ሌላ ፤ ፖለቲካ ሌላ ነው የእኔ መልዕክት፡፡
የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ደግሞ በእንግሊዘኛ መጠቀም መርጠዎል (http://www.ena.gov.et/index.php/economy/item/11520-2017-02-05-17-32-42)፡፡
ምናልባት የመገናኛ ብዙሃን ሪፎርም እየተዘጋጀ ነው ተብሎ የተራገበለት ይኸን ይቀርፍ ይሆን? አብረን እናያለን፡፡ አብራሃም ለቤዛ
Subscribe to:
Posts (Atom)




