Followers

Saturday, May 14, 2016

የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ፤ አሰራት ወልደየስ

የታንዛኒያዉ የነፃነት ታጋይ ፖለቲከኛ እና መምህር (ሙዎሊሙ) ጁሊየስ ኔሬሬ በአንድ ወቅት “I am a schoolmaster by choice and a politician by accident “እንዴት ከሚወደውና ከሚያከብረው ሙያው ተገፍቶ ወደ ፖለቲካ ትግሉ እንደገባ በመግለፅ እንደተናገር ድርሳናት ይጠቅሳሉ፡፡ በነገራችን ላይ ጁሊየስ ኔሬሬ ከአለማችን የትምህርት ፈላስፋዎች ውስጥ ይመደባሉ፡፡

ከላይ ያለዉን ታሪክ ያነሳሁት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆኑት ፐሮፈፌሰር አሰራት ወልየስ  ታሪክ  ከእዉቅ የቀዶ ጥገና ሃኪምነት ዘው አድርጎ  ወደ ፖለቲካዉ እንዲገቡ እንዴት እንዳስገደዳቸው  ለመተረክ ነው፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ በግንቦት 1983 ዓ/ም ማግስት በብሄርተኛ ሃይሎች ተወጥራ ለ3000 ዓመት የገነባችዉ አጋራዊ ድር እየተበጣጠሰ ፤ ዜጎች በሚናገሩት ቋንቋ እየተመዘኑ ከቀያቸው ሲፈናቀሉ፣ ሲታረዱ ፣ ወደ ገደል ሲጣሉ ፤ አንጋፋዉ የህክምና ሊቅ ደራሽ  ያልነበራቸውን ወገኖቻችንን ሰቆቃ ስላንገበገባቸው የህክምና ጋወላቸውን አዉልቀዉ የአባቶቻቸውን ጋሻ እና ጎራዴ አንስተው ተነሱ፡፡ የትግል አጋሮቻቸውን በማሰባሰብ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን እልቂት ለመታደግ ብርቱ ጥረት አድርገዎል፡፡
አስራት እሩህሩህነትንና ደግነትን ከጥልቅ የሙያ አውቀት ጋር የቀሰሙ ሲሆን፤ በሙያቸው ብዙ ሜዳሊያዎችን ከተለያዩ ተቋሞች ተሸልመዎል፡፡ (You can refer the link: Professor Asrat Woldeyes Biography)
አስራት ገና በስምንት ዓመታቸው ወላጅ አባታቸውን በፋሽስት አረመኔያዊ ጭፍጨፋ የተነጠቁት አስራት ፤ የኢትዮጵያ ባህላዊ ትምህርትም የቀሰሙት ከአለቃ ለማ ሃይሉ የኔታነት ነው፤ ድሬደዎ፡፡
ፐሮፌሰር አስራት ያደራጁት መ.አ.ህ.ድ. (መላዉ አምሃራ ህዝብ ድርጅት) አማራን የማዳን አላማ እንግቦ ጠናካራ መሰረት እየያዘ ሲሄድ ፤ ወያኔ/ኢህአዴግ ሰላማዊ ታገዎች ዛሬም ወደ እስር እያጓረ እንደሚገኘዉ አስራትም የእስር ሰለባ ሆነ፡፡ ከዚያማ ፍርድ ቤት ምናምን፡፡
ስንቶችን ከአልጋ ቁራኛነት ከደዌ ዳኛ እናዳልታደገ ፤ የኢትዮጵያን ህክምን ኮሌጅ (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ) እንዳላደራጀ፤ እስረኛው አስራት የእስረኛ አየያዝ ዓለም አቀፍ ህግ ተጥሶ ህክምና እንዳያገኝ ተከለከለ፡፡
ፐሮፌሰር አስራት በእንደዚህ ሁኔታ ነው ግንቦት 6, 1991 ዓ/ም ለህልፈተ ህይወት የተዳረገው፡፡ አስራት ህያው ነህ፡፡ ለተጨቆኑት፤ ለታረዱትና ወደ ገደል ለተወረወሩት ጩኸኻል አልፎም መስዎት ሁነሃልና ሁሌም ህያዉ ነህ፡፡ አንተ ለእኛ ሁሌም ህያው ነህ፤ ትውልዶች ያልፋሉ ነገር ግን ያንተን ፈለግ ተከትለው የሚከተሉህ እልፍ አላፍ ናቸዉና ሁሌም ህያው ነህ፡፡
የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን 17 ሙት ዓመት ስንዘክር ፤ የአስራትን ትክክለኛ አላማ ከግብ ለማድረስ ሁላችንም ለእራሳችች ቃል እንግባ፡፡ ጭቆና፤ አድሎዊነትንና ኢፍታህዊነት በኢትዮጵያ አስወግደን የረዥም አመት ታሪክ ባለቤት የሆነች አጋረችንን ለማየት ያብቃን፡፡ አሜን፡፡


No comments:

Post a Comment