Followers

Wednesday, February 25, 2026

ጉደኛ ሺፈራዎች !! አብራሃም ለቤዛ

 ጉደኛ ሺፈራዎች !!



ሰሞኑን መጀመሪያ አንድ ቪዲዮ አየሁ ፤ አንዱ ሺፈራው ሚኒስተር ዴኢታ ተብየ (ጉራ ፈርዳ አስፈፃሚ) እስስ አሁን ፎርጂድ ካላችሁ መዝግበን እናልፋችሆለን ይላል፤ ሌላው ሺፈራው በጎዳ በር ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ (በኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ አዋጅ ቁጥር 1386/2025 እና በደንብ ቁጥር 576/2025 መሰረት ) ደሃውን ከየትም አምጥተህ ትከፍላታለህ እያለ ነው፡፡


ጉደኛው1 ሺፈራው!!!
______________________

___________________________
ጉደኛው2 ሺፈራው!!!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ……………..ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
ውድ የባንካችን ደንበኞች፤
******
በኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ አዋጅ ቁጥር 1386/2025 እና በደንብ ቁጥር 576/2025 ሁሉም ባንኮች እና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ከሚሰጡት ብድርና ከዲጂታል ባንኪንግ የአገልግሎት ክፍያዎች ላይ በደንቡ ላይ በተቀመጠው ስሌት መሰረት ከደንበኞች ላይ ክፍያዎችን በመሰብሰብ በብሔራዊ ባንከ በተያዘው የኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ ፅ/ቤት ሂሳብ ገቢ እንዲያደርጉ ተደንግጓል፡፡
በመሆኑም ከየካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባንካችን ከሚሰጠው ማንኛውም አይነት መደበኛ ብድር ላይ የሚለቀቀውን መጠን 1% (አንድ በመቶ)፣ እንዲሁም በሁሉም የባንካችን የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎቶች ደንበኞች ከሚከፍሉት የአገልግሎት ክፍያ ላይ 5% (አምስት በመቶ) እየተጨመረ የሚሰበስብ እና ለኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ ፅ/ቤት ገቢ የሚያደርግ መሆኑን በአክብሮት ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ደንበኞች ወደአቅራቢያቸው የሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ ወይም ወደ 951 የደንበኞች አገልግሎት የጥሪ ማዕከል በመደወል መጠየቅ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
*********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!

Wednesday, February 4, 2026

ወልቃይት አማራ-ለቅሶችን አማራ ሰርጋችን አማራ ቋንቋች አማራ በአብራሀም ለቤዛ

 



ስለ ወልቃቴ ግዟት በመጀመሪያ ማንበብ የቻልኩት ከፕሮፌሰር ዓለም እሸቴ ነው፤

እናም ይኸ ግጥም መታሰቢያነቱ ለፕሮፌሰር ዓለም እሸቴ ነው፡፡

ወልቃይት አማራ-ለቅሶችን አማራ ሰርጋችን አማራ ቋንቋች አማራ በአብራሀም ለቤዛ

---------------------------------////--------------------------------

ወልቃይት ፀጋዴ  የአማራዎች ርስት፤

መልካ ምድርሽ ምሽግ  አይመች ለጠላት፤

ወዲያ ከጣሊያን ወዲያ ከደርቡሽ፤

ፍላፃው ይረገፋል  ገና በተራሮችሽ ፤

ወንዞችሽ ተገርተው ሲፈሱ ከሜዳው፤

ተከዜን ጨምሮ ሲሳይ ሆነው ሄደው፤

ሰሊጡና ጥጡ ሃብትሽብ በጉያሽ፤

ስርቶ አዳሪው መጥቶ ቤት የሰራብሽ፤

ወዲያ መዳረሻ  ከተከዜ ማዶ ከራማው ደብር ፤

ፀሎት ሚሰማው ለፈጥኖ ደራሽ ገብርኤል፤

በማህፀንሽ ይዘሽ አበው ገዳምሽን፤

አብረታንት ዋልድባ ቃልኪዳን ያለበት፤

የአባቶችሽ ፀሎት ጠብቆሽ ከመዓት፤

ትህነግ ወያኔ ስግብግነቱ አይሎ ፤

ወልቃይት ገሎ በገፍ አፈናቅሎ፤

ወልቃይት አማራም ጠፋ ጠፋ ሲሉት፤

ወልቃይት አማራ ፤

ለቅሶችን አማራ ሰርጋችን አማራ ቋንቋች አማራ አለና በኩራት፤

የትህነግ  ትዕቢት አስተነፈሰለት፤

ገና ይንሰራራል በሃብትና በእመነት ፤

ወትሮም አባቶቹ ያደሩ ናቸው በእመነት፤

ቋርፍ በልተው ያደረሱት ፀሎት፤

ፈጣሪ ይደርሳል መቼ ይወድቅና ፤

ያ የደም አባላ የማይካድራ ግፍ፤

የንፁሃን እልቂት መቼም አይረሳም ተበዳይ ሳይካስ፤

ትህነግ በሃጢያቶ መች መባዘኖ አበቃ፤

መሆን ስለማራት በሱዳን ተረድታ የጎበዝ አለቃ፤

ሳዳሙሴንም ላይታደጋት ወይም ጋዳፊ ላይመጣ፤

ሞችን እየጠራች  ይኸው ታጣጥራለች፤

Friday, January 30, 2026

ኖሮ ኖሮ ከሞት፤ ዞሮ ዞሮ አዙሪት በአብራሃም ለቤዛ

 


ኖሮ ኖሮ ከሞት፤ ዞሮ ዞሮ አዙሪት

በአብራሃም ለቤዛ

የሜሮን ጌትነትን ግጥም እያዳመጥኩ የፃፍኩት

------------------////----------------------

ያ ስዩም መስፍን  ባድሜ ተሰጠን ፤

የጦር ሜዳ ድሉን በአደባባይ ደገምን፤

ውጣና ተደሰት ዘምባባውን ይዘህ ፤

ተሸከርክና ጨፍር ፈንዲሻህን ደፍተህ፤

የሚል ሳክስ ነበር በቲቪው የነፋው፤

ዲጂታል ሳይበዛ ካድሬና ወረፋው፤

ይኸን ሳንረሳው በዚያኛው ዘመን፤

እነቶኔ ሆነው ከወያኔ ነፃ አውጭ፤

ተረታቸው ሆነ በረጂሙ ትግል ስላደሩት ውጭ፤

ጦርነት አውርደው ደም እንዳላፈሱ፤

በአንዴ እጥፍ ብለው ጲላጦስን ሆነው፤

እኛ መቼ ለኳስን ነው ግፋ በለው ናቸው ብለው አላከኩ ፤

ሰው እንዳለለቀ በነሱ ዳፋ ጦስ፤

እስክስ፤

ይኸው ታረቅን ኢትዮጵያ አሸነፈች፤

አራት ኪሎም አለች፤

ማንም ሳይጠየቅ የሞተ ተጎዳ፤

እንዲሆን ተረቱ የሀገሬው ፍዳ፤

ፕሪቶሪያ ሄደው ፤ሃላላ ተዝናንተው፤

ውስኪ እየተራጩ  አንሶላ ተጋፈው፤

ዛሬም ተመልሰው ይኸው አየናቸው ፤

ከአዙሪቱ ወድቀው፤