Followers

Wednesday, February 4, 2026

ወልቃይት አማራ-ለቅሶችን አማራ ሰርጋችን አማራ ቋንቋች አማራ በአብራሀም ለቤዛ

 



ስለ ወልቃቴ ግዟት በመጀመሪያ ማንበብ የቻልኩት ከፕሮፌሰር ዓለም እሸቴ ነው፤

እናም ይኸ ግጥም መታሰቢያነቱ ለፕሮፌሰር ዓለም እሸቴ ነው፡፡

ወልቃይት አማራ-ለቅሶችን አማራ ሰርጋችን አማራ ቋንቋች አማራ በአብራሀም ለቤዛ

---------------------------------////--------------------------------

ወልቃይት ፀጋዴ  የአማራዎች ርስት፤

መልካ ምድርሽ ምሽግ  አይመች ለጠላት፤

ወዲያ ከጣሊያን ወዲያ ከደርቡሽ፤

ፍላፃው ይረገፋል  ገና በተራሮችሽ ፤

ወንዞችሽ ተገርተው ሲፈሱ ከሜዳው፤

ተከዜን ጨምሮ ሲሳይ ሆነው ሄደው፤

ሰሊጡና ጥጡ ሃብትሽብ በጉያሽ፤

ስርቶ አዳሪው መጥቶ ቤት የሰራብሽ፤

ወዲያ መዳረሻ  ከተከዜ ማዶ ከራማው ደብር ፤

ፀሎት ሚሰማው ለፈጥኖ ደራሽ ገብርኤል፤

በማህፀንሽ ይዘሽ አበው ገዳምሽን፤

አብረታንት ዋልድባ ቃልኪዳን ያለበት፤

የአባቶችሽ ፀሎት ጠብቆሽ ከመዓት፤

ትህነግ ወያኔ ስግብግነቱ አይሎ ፤

ወልቃይት ገሎ በገፍ አፈናቅሎ፤

ወልቃይት አማራም ጠፋ ጠፋ ሲሉት፤

ወልቃይት አማራ ፤

ለቅሶችን አማራ ሰርጋችን አማራ ቋንቋች አማራ አለና በኩራት፤

የትህነግ  ትዕቢት አስተነፈሰለት፤

ገና ይንሰራራል በሃብትና በእመነት ፤

ወትሮም አባቶቹ ያደሩ ናቸው በእመነት፤

ቋርፍ በልተው ያደረሱት ፀሎት፤

ፈጣሪ ይደርሳል መቼ ይወድቅና ፤

ያ የደም አባላ የማይካድራ ግፍ፤

የንፁሃን እልቂት መቼም አይረሳም ተበዳይ ሳይካስ፤

ትህነግ በሃጢያቶ መች መባዘኖ አበቃ፤

መሆን ስለማራት በሱዳን ተረድታ የጎበዝ አለቃ፤

ሳዳሙሴንም ላይታደጋት ወይም ጋዳፊ ላይመጣ፤

ሞችን እየጠራች  ይኸው ታጣጥራለች፤

No comments:

Post a Comment