Followers

Wednesday, February 25, 2026

ጉደኛ ሺፈራዎች !! አብራሃም ለቤዛ

 ጉደኛ ሺፈራዎች !!



ሰሞኑን መጀመሪያ አንድ ቪዲዮ አየሁ ፤ አንዱ ሺፈራው ሚኒስተር ዴኢታ ተብየ (ጉራ ፈርዳ አስፈፃሚ) እስስ አሁን ፎርጂድ ካላችሁ መዝግበን እናልፋችሆለን ይላል፤ ሌላው ሺፈራው በጎዳ በር ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ (በኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ አዋጅ ቁጥር 1386/2025 እና በደንብ ቁጥር 576/2025 መሰረት ) ደሃውን ከየትም አምጥተህ ትከፍላታለህ እያለ ነው፡፡


ጉደኛው1 ሺፈራው!!!

______________________

___________________________
ጉደኛው2 ሺፈራው!!!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ……………..ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
ውድ የባንካችን ደንበኞች፤
******
በኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ አዋጅ ቁጥር 1386/2025 እና በደንብ ቁጥር 576/2025 ሁሉም ባንኮች እና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ከሚሰጡት ብድርና ከዲጂታል ባንኪንግ የአገልግሎት ክፍያዎች ላይ በደንቡ ላይ በተቀመጠው ስሌት መሰረት ከደንበኞች ላይ ክፍያዎችን በመሰብሰብ በብሔራዊ ባንከ በተያዘው የኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ ፅ/ቤት ሂሳብ ገቢ እንዲያደርጉ ተደንግጓል፡፡
በመሆኑም ከየካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባንካችን ከሚሰጠው ማንኛውም አይነት መደበኛ ብድር ላይ የሚለቀቀውን መጠን 1% (አንድ በመቶ)፣ እንዲሁም በሁሉም የባንካችን የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎቶች ደንበኞች ከሚከፍሉት የአገልግሎት ክፍያ ላይ 5% (አምስት በመቶ) እየተጨመረ የሚሰበስብ እና ለኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ ፅ/ቤት ገቢ የሚያደርግ መሆኑን በአክብሮት ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ደንበኞች ወደአቅራቢያቸው የሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ ወይም ወደ 951 የደንበኞች አገልግሎት የጥሪ ማዕከል በመደወል መጠየቅ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
*********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!

No comments:

Post a Comment